Thursday 22 December 2016

የወልቃይትና ያለውደታቸው ወደ ትግራይ የተጠቃለሉ ወረዳዎች ጥያቄ ምላሽ የሚያገኘው ህወሃት ከሥልጣን ሲወገድ ብቻ ነው።



December 18, 2016
Dec 17, 2016
አርበኞች ግንቦት 7 የህወሃት አገዛዝ ካልተወገደ በቀር ላለፉት 25 አመታት በአገራችን የሰፈነው ዘረፈ ብዙ ችግሮች አይወገድም ብሎ ከሚያምንባቸው ምክንያቶች አንዱ ቋንቋንና ባህልን መስፈርት ባደረገ አከላለል ተፋቅሮና ተከባብሮ ይኖር የነበረ ህዝብ መካከል የተዘራው የመከፋፈልና የጠላትነት ስሜት ውሎ አድሮ ህዝባችንን ወደ ከፋ የርስ በርስ ጦርነት እንዳይወስዳት ለመከላከልና አገራችንንም ከመበታተን አደጋ ለመታደግ ነው።
ኢትዮጵያን እንደ አንድ አገር ህዝቦቿንም በታሪክና በመልካ ምድር ብቻ ሳይሆን በባህል፤ በቋንቋና በስነልቦና የተቆራኙ መሆናቸውን እውቅና መስጠት ለማይፈልግ ዘረኛው የህወሃት ቡድን ከትግራይ ውጪ ያለው ለምና በተፈጥሮ ሃብት የበለጸጉ ቦታዎች በሙሉ እንደ ባዕድ ሃብት የሚቆጠሩና የጠላት ይዞታዎች ናቸው። በዚህም እምነቱ የተነሳ የመንግሥት ሥልጣን በተቆጣጠረ ማግሥት ከትግራይ ጋር የሚዋሰኑ ለምና ድንግል የሆኑ መሬቶችን በከፍል ወይም በሙሉ ወደ ትግራይ ጠቅልሎአቸዋል። ከወራት በፊት ጎንደር ውስጥ ለተቀሰቀሰውና ወደ ጎጃም ለተዛመተው ህዝባዊ እምቢተኝነት ምክንያት የሆነው የወልቃይት ጠገዴ መሬት ላለፉት 25 አመታት የትግራይ አካል እንዲሆን የተደረገው በዚህ አይነት ያፈጠጠና ያገጠጠ የጠላትነት ስሜት ነው፡፡ ወልቃይት ጠገዴ ጎንደርን ከትግራይ ጋር ብቻ ሳይሆን ከኤርትራና ከሱዳን የሚያዋስን በታሪክ የጎንደር ግዛት አካል መሆኑን በንጉሱ ነገሥቱ ዘመን ትግራይን ለአመታት ያስተዳደሩት ልዑል ራስ መንገሻ ስዩም በአደባባይ የመሰከሩት እውነታ ነው። ህወሃት አሁን የአማራ ክልል ብሎ ከሚጠራው የትግራይ አዋሳኝ ቦታዎች መሬት የቀማው ከጎንደር ብቻ አይደለም።
በወሎና በአፋር በኩልም እንዲሁ ኮረም፤ ራያ ፤ አበርጌሌ፤ ስሄሎ፤ ጎዶሌ፤ ታላክ፤ ሳውኔ ወይም ጊሊስ የተባሉ ወረዳዎች ተጠቃለው ትግራይ ውስጥ እንዲካለሉ ተደርገዋል። በህወሃት የአገዛዝ ዘመን ወደ ትግራይ እንዲካለሉ የተደረጉ እነዚህ ከላይ የተጠቀሱ ቦታዎች በሙሉ በተፈጥሮ ለምነታቸው ወይም የተለያዩ የከበሩ ማዕድናትን በከርሰ ምድራቸው በመያዝ የሚታወቁ ናቸው። እነዚህን ለምና ድንግል ቦታዎች ቀምቶ ለዘመናት የኢትዮጵያ ታሪክ ማዕከል የሆነቺውን ትግራይ በቆዳ ስፋት ለማሳደግ ህወሃት ለምን እንደተጣደፈ ለማወቅ ሰፊና ረዥም ጥናት የሚጠይቅ እንቆቅልሽ የለውም።ኢትዮጵያችንን የመግዛት አቅሙ ከተመናመነና ከሥልጣን ከተባረረ በህገ መንግሥቱ ያሠፈረውን የመገንጠል መብት ተጠቅሞ ገና ከበረሃ የትግል ዘመኑ ጀምሮ በራዕዩ ያስቀመጣትን ታላቋን የትግራይ ሪፑብሊክ መሥርቶ የዘረፈውን ሃብትና ንብረት ለመብላት ዕድል የሚያገኝ ስለሚመስለው ነው። ከትውልድ መንደራቸው ውጪ ያለው ህዝብና አገር ለማይታያቸው ለነ ሳሞራ ይኑስ አይነቶቹ እብሪተኞች የታላቋ ትግራይ ምሥረታ ጉዳይ ህልም ሳይሆን በተፈለገበት ሰዓት መተግበር የሚቻል በእጅ ያለ እውነት ነው።
አርበኞች ግንቦት 7 የህወሃት መሪዎች የፈለጉትን ሁሉ በጉልበት ህዝብ ላይ መጫን የሚችሉ በአገራችን ጉዳይ ብቸኛ አድራጊና ፈጣሪ አድርገው እራሳቸውን እንዲመለከቱ ያስቻላቸው የኛ የህዝቦቿ ትዕግሥትና ዝም ባይነት ነው ብሎ ያምናል። ዛሬ ህዝባዊ እምቢተኝነትን የቀሰቀሰው የወልቃይት ጠገዴ መሬት በጉልበት ተቀምቶ ተወላጆቿ ለአመታት ሲፈናቀሉና በህወሃት ታጋዮችና ታማኝ አገልጋዮች የነዋሪዎች አሠፋፈር ገጽታዋ ሲቀየር ዝም ብለን መመልከታችን ከምን አይነት ችግር ውስጥ እንደከተተን ያልተረዳ የለም። እናም የወልቃይት ህዝብ ያነሳው የማንነት ጥያቄ አስቸኳይ መፍትሄ እንዲያገኝና ከወሎና ከአፋር ያለውዴታቸው ወደ ትግራይ እንዲካለሉ የተደረጉ ነዋሪዎች ፍላጎት ምን እንደሆነ እንዲታወቅ ህዝባዊ ወያኔ ሃርነት ትግራይ ወይም በተለምዶ ስሙ የወያኔ አገዛዝ በአስቸኳይ ማብቃት አለበት።
አርበኞች ግንቦት 7 የወልቃይት ህዝብ እየታገለለት ያለውን ዓላማ ከልብ የሚደግፍ ብቻ ሳይሆን ጥያቄው ምላሽ እንዲያገኝ ባለው አቅሙ ሁሉ ይፋለማል። ንቅናቄያችን በሚያካሂደው ሁለገብ ትግል አገራችን ውስጥ ፍትህ እኩልነትና ነጻነት የሠፈነበት የዲሞክራሲ ሥርዓት ሲገነባ ኢትዮጵያዊያን ሁሉ ህወሃት
ከዘረጋው የዘር ልዩነቶችና ክፍፍሎች በላይ በዜግነታቸው ገዝፈው የሚታዩበት የበለጸገችና አንደነቷ የተከበረች አገር ባለቤት ይሆናሉ ብሎ ያምናል።
ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ !

Thursday 1 December 2016

Ethiopia's Merera Gudina detained after trip to Europe


Ethiopia's Merera Gudina detained after trip to Europe

  • 4 hours ago
  •  
  • From the sectionAfrica

Ethiopian opposition leader Merara GudinaImage copyrightAFP
Image captionMerera Gudina's arrest has been criticised by a member of the European parliament

A prominent opposition leader in Ethiopia has been detained after he returned from Europe.
Merera Gudina had violated Ethiopia's state of emergency by having contact with "terrorist" and "anti-peace" groups, state-linked media reported.
Mr Merera criticised the state of emergency in an address to the European parliament on 9 November.
The government imposed it in October to end an unprecedented wave of protests against its 25-year rule.
More than 11,000 people have since been arrested.
Mr Merera, who is the leader of the Oromo Federalist Conference, was arrested on Wednesday at the airport in the capital, Addis Ababa, after he flew in from Brussels, reports BBC Ethiopia correspondent Emmanuel Igunza.
Several of his relatives who were with him were also detained, local media report.
European parliament member Ana Maria Gomes, who invited Mr Merera, told the BBC she was "extremely shocked" about the arrests.
She said she would push for the European Union take a tougher line against the Ethiopian government.

Ethiopian runner Feyisa Lilesa making a Oromo protest gesture at the OlympicsImage copyrightAFP
Image captionAthlete Feyisa Lilesa brought global attention to the situation in Ethiopia with his protest at the Olympics

Mr Merera has previously criticised the arrests of hundreds of people from the Oromo and Amhara ethnic groups, which were at the forefront of anti-government protests.
The meeting at the European parliament was also attended by Ethiopia's Olympic medallist Feyisa Lilesa.
He refused to return home after the Rio Games, saying his life would be in danger.
The marathon runner crossed the line in second place with his arms above his head in solidarity with Oromo activists.
Mr Merera had served seven years in prison for opposing the former regime of Mengistu Haile Mariam.
He also took part in the overthrow of Ethiopia's last emperor, Haile Selassie.
Many people in the Oromo and Amhara ethnics groups, two of the largest in Ethiopia, complain of political and economic marginalisation.