Wednesday 25 February 2015

መልእክት ለወጣቶች፤ (በወጣቶች ጉዳይ መምርያ)


patriots-ginbot-7-youth-prወጣት ለአገር እድገትና ብልጽግና የሚያበረክተው አስትዋጾ ከፍተኛና በቀላሉ ለውጥ ማምጣት የሚችል ኃይል ያለው የህብረተሰብ ክፍል መሆኑ ይታወቃል። ይህን በቀላሉ ለውጥ ማምጣት የሚችል ትውልድ ጊዜው በሚጠይቀውና ለአገራችን በሚበጅ መልኩ ማደራጀት፣ መምራትና ንቅናቄው ለሚያደርገው የነጻነት፣ የፍትህና ዲሞክራሲ ትግል ግንባር ቀደም ሁኖ እንዲሰለፍ ማስቻል የንቅናቄያችን አርበኞች ግንቦት ሰባት ዋና ተግባር ነው። ስለሆነም ንቅናቄያችን ወጣቱ ትውልድ ለአገር እድገትና ዲሞክራሲያዊ ግንባታ የያበረክተው አስትዋጾ ከፍተኛና አስፈላጊ መሆኑን ግንዛቤ ውስጥ በማስገባት የወጣቶች ጉዳይ መምሪያን አቋቁሞ ወጣቱን የህብረተሰብ ክፍል ትግሉን እንዲቀላቀል በማድረግ ላይ ይገኛል።
መምርያው የተቋቋመበት ዋና ዓላማ ወጣቱ ትውልድ የወያኔን ፈላጭ ቆራጭ አገዛዝ፣ ኢ_ዲሞክራሲ፣ ኢ_ሰባዊ ድርጊት እና የሚያራምደውን የዘር ፖለቲካ በአጠቃላይ የወያኔን አምባገነናዊ ስርዓት በሚገባ እንዲገነዘብ በማድረግ እንዲሁም የንቅናቄያችንን ዓላማና ግብ በማስረዳት ለነጻነት፣ ፍትህና ዲሞክራሲ ለሚደረገው የሁለገብ ትግል ወጣቱ ትውልድ ድርሻውን እንዲወጣ ማድረግ እና ኢትዮጵያ አገራችንን ጠብቆና አስከብሮ ለትውልድ የማስተላለፉን ኃላፊነት እንዲረከብ ማስቻል ነው።
እንደሚታወቀው የአንድ አገር ቀጣይነት ያለው እድገት የሚለካው በአላት መሠረተ ልማት፣ ቁሳዊ ሃብትና ንብረት ብቻ ሳይሆን በዋናነት ይህን ተረክቦ በአደራ ለትውልድ ማስተላለፍ የሚችል ትውልዳዊ ትስስር ሲኖር ነው። ይህንንም የአገርና የህዝብ አደራ ድልድይ ሆኖ ከትውልድ ወደ ቀጣዩ ትውልድ የሚያስተላልፍ ወጣቱ የህብረተሰብ ክፍል ስለሆነ ኢትዮጵያን ከወያኔ የጨለማ ቡድን መታደግ ለነገ የማይባይል አገራዊ ግዴታ መሆኑን ተገንዝቦ ወጣቱ ትውልድ ኃይሉንና አቅሙን ተጠቅሞ የእራሱን ነጻነት በእራሱ ማወጅ እንደሚችል መምርያው ያሳስባል።
በማንኛውም አገር፣ ጊዜና ዘመን እያንዳንዱ ትውልድ የአገሩ ወራሽ፣ ተተኪና ተረካቢ፣ ጠባቂና ለሚቀጥለውም ትውልድ የማውረስ፣ የማስተላልፍና የማስረከብ ኃላፊነትና ግደታ አለበት። ስለሆነም አገርን ከእነ ሙሉ ክብራ ለሚቀጥለው ትውልድ ማስተላለፍ የእኛ የወጣቶች የዜግነት ግዴታ መሆኑን ተረድተን ጥልቅ በሆነ አገራዊ ስሜት በሦስቱም ዘርፍ ማለትም በማህበራዊ፣ በምጣኔ ሃብታዊና በፖለቲካዊ ጉዳዮች ላይ ከፍተኛ አገራዊ ተጽዕኖ ማድረግ እንደሚቻል በእርግጠኝነት የወጣቶች ጉዳይ መምርያ በድጋሚ በአጽንኦት ያሳስባል።
ውድ የአገራችን ወጣቶች ሆይ፤
የምንወዳትና የምንሳሳላት ብርቅዬ የጀግኖች አገር ኢትዮጵያ በባንዳዎች ወያኔ ለ24 ዓመታት የጥፋት ዘመቻ እየተካሄደና እየተፈጸመባት ሉዓላዊነቷ ተንቆ ትገኛለች። አምባገነኑ የወያኔ ቡድን በጠበንጃ ኃይል ስልጣን ከያዘበት ጀምሮ ሰብአዊ መብታችን ተጥሶ፣ ዲሞክራሲያዊ መብት ተነፍጎን፣ ተፈጥሮአዊ መብታችን ተነጥቆ፣ የዜግነት ማንነታችን ባንዲራችን ሳይቀር ተቀይሮ፣ ብሔራዊ ሃብትና ንብረት እየተዘረፈ፣ የአገራችን አርሶ አደር ለም መሬቱ እየተሸጠ፣ እተነጠቀና እየተባረረ፣ ለአገር የሚታገለው ንጹህ ዜጋ ፀረ ሰላም ፀረ ህግ ፀረ መንግሥት በመባል የሽብርተኛ ሕግ ወጥቶለት እየታሰረ፣እየተገደለና እየሞተ፣ እየተፈናቀለና እየተሰደደ፣ በግፍና በጭቆና ላይ መሆኑን ለአንተ ንቁ ህልሊና ላለህ ወጣት ትውልድ የተሰወረ አይደለምና በጽኑ በአስቸኳይ ታገለው። ነጻነትን አውጅ፤ ፍትህን ተቀዳጅ!ታሪክህን መልስ! ወያኔን ይብቃህ ከህዝብ ላይ ውረድ በለው።
ውድ የአገራችን ወጣቶች ሆይ፤
አገራችን ኢትዮጵያ ለብዙ ሺህ ዘመናት በነፃነት በቀደሙ አባቶቻችን ተጠብቃ የቆየችው በአካልና በደም ዋጋ ነው። በዚህም የኢትዮጵያ ሕዝብ ቆራጥነትና ፅናት አገርን በነፃነት መጠበቅ በዓለም ፊት ትልቅ ምሳሌነትን ያተረፈ፣ ዛሬ ለአለነውና ለመጭውም ትውልድ የሚኰራበት ሕያው የታሪክ አለኝታ፣ መመኪና ክብር ያለን ውድ ህዝቦች ነን። ይህ አኩሪ ታሪክ ፣ የዘላለም ሃብታችን በመሆኑ ጠብቀንና አስከብረን ለትውልድ ለማስረከብ ኃላፊነቱ በዋናነት የእኛ ወጣቱ ነው። ይህን እውነታ ተቀብሎ አገርን በነፃነት ለመጠበቅ ደፋ ቀና ከሚሉ ኢትዮጵያውያን ጋር አገራዊ ኃላፊነትንና ግዴታን ለመወጣት ዝግጁና ብቁ ሆኖ መታገል በእጅጉ ያስፈልጋል። ስለዚህ የአገራችን ወጣት ሁላችሁ ሰላም፣ ነጻነት፣ ፍትህና ዲሞክራሲ የሰፈነባት ኢትዮጵያን ለመገንባትና አገራዊ ድርሻንም ለመወጣት በህብረት ተነስ!፣ ታጠቅ!፣ ሰው ሁን! ታሪክህን መልስ!አረመኔው ወያኔን በቃህ በለው!
በአጠቃላይ እኛ ወጣቶች ለአገር ነጻነት፣ ፍትህና ዲሞክራሲ ለሚደረገው ትግል የወጣትነትን አቅምና ኃይል ተጠቅመን የታሪክ ባለቤት እንሆን ዘንድ በሁለገብ ትግል የኢትዮጵያን ጠላት ወያኔን ለማስወገድ ከሚታገለው አርበኞች ግንቦት ሰባት ለአንድነትና ለዲሞክራሲ ንቅናቄ ጋር በመቆም ሰላም፣ ነጻነት፣ ፍትህና ዲሞክራሲ የሰፈነባት ኢትዮጵያን ለመገንባት እና በጽናት አረመኔው ወያኔን ከህዝባችን ጫንቃ ላይ ለማስወገድ የበኩላችንን ኃላፊነትና ግዴታ መወጣት አለብን።
እንዲሁም አገር ወዳድ ኢትዮጵያውያን አገራችን የጣለችብንንና የሚጠበቅብንን አገራዊ ኃላፊነት በትጋትና በንቃት መወጣት የሁላችንም ግዴታ መሆኑን ተገንዝበን ለአገር እድገት የጀርባ አጥንት የሆነውን የህብረተሰብ ክፍል ወጣቱን ከወያኔ ትውልድ ገዳይና አገር ሻጭ አገዛዝ መታደግ ተቀዳሚ ተግባር በማድረግ ትግላችንን ይበልጥ ማጠናከር እንዳለብን በጥብቅ ለማሳሰብ እንወዳለን።
ወጣቱ ትውልድ ጊዜውን፣ ኃይሉን፣አቅሙንና ጉልበቱን ተጠቅሞ ለአገርና ለእራሱ ነጻነት እንዲታገል ምቹ ሁኔታወችን መፍጠር፣ ወኔና አገራዊ ስሜት እንዲኖረው መቀስቀስ፣ ወጣቱ ትውልድ በንቃትና በቁርጠኝነት ትግሉን በባለቤትነት ተረክቦ የድልና የነጻነት ዓርማ እንዲያውለበልብ ማድረግና ጥቅሙንም ማስገንዘብ የሁሉም የህብረተሰብ ክፍል አገራዊ ተግባርና ኃላፊነት መሆኑን ተገንዝበን ሁላችንም ወጣቱን ትውልድ ከወያኔ ለመታደግ የድርሻችንን መወጣት ይኖርብናል።
በመጨረሻም ዘመኑ በአፈራቸው የብዙኃን መገናኛ መንገዶች በመጠቀም ለወጣቶች ወጣት ተኮር መልክቶችን በቀጣይነት ማስተላለፈ ስለተፈለገ በማነኛውም መንገድ ወጣቱን ለትግል ሊያነቃቃና አገራዊ እውቀት ሊያስጨብጥ የሚችል ግብዓት በመስጠት ትውልድ የማዳንና የማፍራት ተልእኮን እንድትጋሩ የወጣቶች ጉዳይ መምሪያ መልእክቱን በአክብሮት ያስተላልፋል።
ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ!
የአርበኞች ግንቦት 7 ወጣቶች ጉዳይ መምርያ

ከህወሃት ምርጫ የሚገኘው ትርፍ ውርደት ብቻ ነው


pg7-logoህወሃት ኢሕአዴግ የተባለውን ጭንብል አጥልቆ አገሪቷን ሙሉ በሙሉ በቁጥጥሩ ሥር ካስገባ ግዜ ጀምሮ በኢትዮጵያዊያን ላይ የተፈፀሙ ወንጀሎች ፈርጀ ብዙ ናቸው። እነዚህ ፈርጀ ብዙ ወንጀሎች በልዩ ልዩ ተቋማት እና ግለሰቦች በማስረጃ ተደግፈው ተመዝግበው ተቀምጠዋል። ከሰሞኑ እንኳ በአውሮፓ ህብረት ውስጥ በተደረገው አንድ ጉባኤ ላይ ግራሃም ፔብል የተባሉ ታዋቂ ሰው ህወሃቶች የፈፀሟቸውን ወንጀሎች በማስረጃ አስደግፈው ከዘረዘሩ በኋላ ህወሃት “አሸባሪ መንግስት” ነው ብለዋል። ይሄ እውነት ነው። ኢትዮጵያ ከአምባገነን ገዥዎች ተላቃ የምታውቅ አገር አለመሆኗ የታወቀ ቢሆንም እንደ ህወሃት ያለ የህዝብ ጠላት መሆንን መርጦ የገዛ ህዝቡን የሚያሸብር መንግስት ነኝ የሚል አካል ግን አልታየም።
ህወሃት አሸባሪ ነው። ይሄ አሸባሪ ቡድን በሚያካሂደው ምርጫ ውስጥ የተሳተፈ ሁሉ እድል ፈንታው ውርደት፤ እስራት፤ ስደት እና ግዲያ መሆኑን እሰክ ዛሬ በተካሄዱት ምርጫዎች አይተናል። ህወሃት ኢሕአዴግ የተባለውን ጭንብል አጥልቆ በምርጫ ሰበብ የብዙ ንፁህን ዜጎችን ደም አፍስሷል። በምርጫ ሰበብ ያፈረሰው ቤት፤ የበተነው ቤተሰብ ብዙ ነው። አገራችን በፖለቲካ እስረኞች ብዛት አቻ ያልተገኘላት ሁናለች። በስደተኛ ብዛትም የመሪነቱን ደረጃ ይዛለች። ይህን ሁሉ ግፍ ያዩ የውጭ ታዛቢዎች ኢትዮጵያን ከውዳቂ አገራት መካከል መድበዋታል።
ህወሃቶች በታሪክ አጋጣሚ ከተቆናጠጡበት ወንበር ከሚወርዱ ሞታቸውን እንደሚመርጡ ደጋግመው በአደባባይ ተናግረዋል። ለዚህም እነርሱ ምክንያት የሚሉት ይህን ወንበር ያገኘነው በደማችን ነው። በደም ያገኘነውንም ወንበር እንዲሁ የምናስረክብ አይደለንም ይላሉ። ወንበሩን አንለቅም ብለው ቢያቆሙ መልካም ነበር፤ ወንበሩን የምንለቅ ከሆነ አገሪቷን እንበትናታለን የሚለውን ነውር ሃሰብ ማቀንቀናቸው ደግሞ ህወሃቶቹ አንዳች ዓይነት የአዕምሮ ቀውስ ውስጥ መግባታቸውን ያመለክታል። የእነዚህን ቡድኖች ነውረኛነት በ1997 ዓ.ም በተደረገው ምርጫ ደህና አድርገን ታዝበናል። በሌብነት እና በሌላ ነውር ምክንያት ከድርጅቱ የተባረሩት ሳይቀሩ ተሰባስበው ህወሃትን ለማዳን የሚል የጥፋት ዘመቻ በአገሪቷ ላይ መክፈታቸው የሚረሳ አይደለም። ህወሃት ወንበሩን የሚለቅ ከሆነ ተመልሰን ወደ ጫካ እንገባለን ማለታቸው የአደባባይ ሚስጢር መሆኑም የሚረሳ አይደለም።
እስከ አሁን በተደረገው ምርጫ የኢትዮጵያ ህዝብ ያተረፈው ነገር ቢኖር ውርደት እንጂ ክብር አይደለም። ህወሃቶች ምርጫ እያሉ ህዝቡን እያዋረዱ፤ የአገሪቷንም ሃብት እየበዘበዙ፤ እነርሱ ከህግ በላይ ሌላው ከእነርሱ ጫማ ስር ሁኖ የሚኖርበትን ሥርዓት እየሰሩ ኑረዋል። ይህ እነርሱ ለእነርሱ የሠሩት ሥርዓት እንዲሁ እንዲለወጥ ይፈልጋሉ ብሎ ከማሰብ የምናተርፈው ነገር ቢኖር ውርደት ብቻ ነው። ህወሃቶች የተፈጠሩበትም ምክንያት አገሪቷንና ህዝቧን ለማዋረድ ነው ለማለት የሚያስችሉን ከበቂ በላይ ምክንያቶች አሉ።
ህወሃቶች እንደ ጤነኛ ሰው ለማሰብ የሚያስችላቸው ስብዕና የሌላቸው መሆኑ ይታወቃል። እኛ ከስልጣን የምንወርድ ከሆነ አገሪቷን እንበትናታለን በሚል ቅዥት ውስጥ የመገኘታቸው ምስጢርም የስብዕናቸውን የዝቅጠት ደረጃ የሚያመላክት ነው።በሰላማዊ መንገድ ተወዳድረው እና ተመርጠው ስልጣን ለመያዝ በጎ ራዕይ ያላቸውን ሁሉ በጠላትነት ፈርጀው እና የአሸባሪነት ካባ ደርበውላቸው በጎ ራዕያቸውን እያመከኑ እንደሆነ እያየን ነው። አሁን በአንድነት እና በመኢህአድ ላይ የተወሰደው እርምጃ የዜጎችን በጎ ራዕይ የማምከን ተግባር መገለጫ ሁኖ ሊጠቀስ ይችላል። ህወሃቶች ራዕይ አልባ ናቸው።ለኢትዮጵያ በጎ ራዕይ ቢኖራቸው ኑሮ “እኛ ከሌለን አገሪቷን እንበትናታለን” አይሉም ነበር። ራዕይ ያለው ከእኔ የተሻለ ካለ ይሥራ ይላል እንጂ እኔ ካልሆንኩ ሞቼ እገኛለሁ አይልም። ህወሃቶች ቅዥታቸውን ራዕይ ብለው ይጠራሉ። በቅዥት ዓለም ውስጥም እንደሚኖሩ የሚነገራቸው ከተገኘም ዘራፍ ብለው አሸባሪ ይላሉ እንጂ ለማድመጥ ችሎታ እና ትዕግስት የላቸውም።
እንግዲህ ህወሃቶች ኢሕአዴግ የተባለውን የምናምንቴዎችን ስብሰብ ጭንብል አጥልቀው በሚያካሂዱት ምርጫ ላይ የተሳተፈ ሁሉ ያተረፈው ውርደት መሆኑን እናውቃለን። ይሄን ውርደት መምረጥ ትክክለኛ ምርጫ ሊሆን አይችልም። ህወሃት የያዘው ስልጣን የነብር ጭራ ሁኖበታል። የነብሩን ጭራ ከለቅኩ ደግሞ እጠፋለሁ የሚል ፍርሃት ውስጥ ወድቋል። ከዚህ ውድቀት ለመነሳት የሚያስችል እውቀትና ቅንነት ስለሌለው ጥላው እያስበረገገው መኖር ግድ ሁኖበታል። ይሄ በርጋጋ ቡድን በኢትዮጵያዊያን ላይ የፈፀመው ወንጀል በሰላማዊ መንገድ በሚደረግ ምርጫ ስልጣኑን እንዲለቅ ያደርገዋል የሚል እምነት የለንም። ይሄ ቡድን ካፈጣጠሩ ጀምሮ ቂመኛና ምህረትን የማያውቅ በመሆኑ ሌሎችንም የሚያየው ራሱን በሚያየው ዓይኑ ነው። ይሄ ቡድን ከራሱ ክበብ ወጥቶ በተለየ እና በተሻለ ሁኔታ ለማሰብ ቅንነት ስለሌለው ሁሉም ሰው እርሱ ራሱን ይመስለዋል። ይሄ ቡድን በዚህ መንፈስ ሁኖ በሚያካሂደው ምርጫ ውስጥ መሳተፍ ትክክለኛ አካሄድ ስለማይሆን ምርጫውን ህወሃትን ከመሠረቱ ለመቀየር መጠቀም ተገቢ አካሄድ ይሆናል። ምርጫው ህወሃትን ከሥሩ የማይቀይረው ከሆነ ይህ ዘረኛና ዘራፊ ቡድን ለሌሎች ማሳየት የሚፈልገውን ህጋዊ ሽፋን በማግኘት በጥፋት ጎዳናው እንዲቆይ ያደርገዋል።
የኢትዮጵያ ህዝብ ሆይ !
ህወሃቶች አገሪቷን ከተቆጣጠሩ ዘመን ጀምሮ ከተደረጉት ምርጫዎች ያተርፍከው ውርደት ነው። ህወሃቶች ምርጫ እያካሄዱ ልጆችህን ይቀጠቅጣሉ፤ ይገድላሉ። ምርጫ ብለው ሲያበቁ አልመረጥከኝም ብለው መሬትህን ይነጥቃሉ፤ ከአቅምህ በላይ ግብር ይጥሉብሃል። ናና ምረጥ ብለው ሲያበቁ አልመረጥከኝም ብለው ከሥራህ ያባርሩሃል፤ ቤተሰቦችህንም ይበትናሉ። ህወሃቶች ምርጫ በሚሉት ቧልት የደረሰብህ ውርደት ብዙ ነው። እንግዲህ በህወሃቶች ምርጫ የምትሳተፍ ከሆነ እስከ ዛሬ ሲፈፀም የቆየውን ውርደት ለመጨረሻ ግዜ በቃ ልትለው ቆርጠህ ተነሳ። ህወሃቶች የኢትዮጵያ ጠላት መሆንን የመረጡ ቡድኖች ናቸው። የራስህን ጠላት በራስህ ላይ መርጠህ እንዳትሾም ለራስህ ተጠንቀቅ።
እኛ አርበኞች-ግንቦት ሰባት የአንድነትና የዴሞክራሲ ንቅናቄ ህወሃት በሰለጠነ መንገድ በሚደረግ የፖለቲካ ውድድር ውስጥ ገብቶ ለመፎካከር ችሎታ እንደሌለው አይተናል። ችሎታ ብቻ ሳይሆን ቅንነትም የሌለው ክፉ ቡድን መሆኑንም እናውቃለን። ህወሃት የጨበጥኩትን ስልጣን የምለቀው “በሬሳየ ላይ ነው” ያለው ሃሳብ የያዝነውን የትግል መንገድ እንድንመርጥ አድርጎናል። ህወሃትም ”ሞት ወይም ስልጣን ላይ መቆየት” የሚል የማይናወፅ እምነቱ እንዲሁ በዋዛ እንደማይቀየር አበክሮ ነግሮናል። እነዚህ ቡድኖች በጎ የሆነ አገራዊ ራዕይ ኑሯቸው እና የዜጎችን ብሄራዊ ስሜት አጠናክረው አገሪቷን በአንድነት ለመምራት በጎ ምኞት ቢኖራቸው ኑሮ በስልጣን ላይ ለመቆየት ቢሟገቱ ግድ ባላላን ነበር። እነርሱ ግን አገር እያፈረሱ፤ በየእለቱ የንፁህ ዜጋ ደም እያፈሰሱ፤ ወጣቱን ለስደት እየዳረጉ፤ ገበሬውን መሬት አልባ አድርገው የአረብና የህንድ ባሪያ እያደረጉት፤ ቀና ብሎ ያያቸውን ሁሉ አሸባሪ እያሉ ለእስር እየዳረጉ፤ ብዙ ዜጎችን አገር አልባ አድርገው እያየን ዝም ለማለት ሰው መሆናችን አይፈቅድልንም። በሚገባቸው ቋንቋ ልናናግራቸው ተዘጋጅተናል። ብዙ ወጣቶች ከመላው የአገሪቷ ክፍሎች ህወሃቶች የገነቡትን የዘረኝነት አጥር እያፈረሱ ወደ ትግሉ እየተቀላቀሉ ነው። በእኛ ዘንድ ማንነታችን ኢትዮጵያዊነት እንጂ ሌላ መሰፍረት አይደለም። ኢትዮጵያዊነት በቀይ ቀለም በልባችን ውስጥ የተቀረፀ የምንሰዋለት ማህተማችን ሁኗል።
በህወሃት ዘመን ስሟ የጎደፈው ኢትዮጵያችንን ስሟን በደማቅ ብዕር ልንፅፍ ተነስተናል። ኢትዮጵያን ወደ ቀደመው ክብሯ ልንመልሳት አያቶቻችን በተመላለሱበት ተራራ ላይ ተሰማርተናል። ኢትዮጵያችን እንደ ነብር የተዋበ ዥንጉርጉርነቷን እንደያዘች የታፈረች አገር ሁና ስሟ እንዲነሳ ለማድረግ የሚያስችለንን የትግል ስልት መርጠናል። ወጣቶቿ የማይሰደዱባት፤ዜጎቿ በልተው የሚያድሩባት፤ ምሁራኖቿ እውቀታቸውን ያለ ገደብ የሚያፈሱባት፤ ነጋዴዎች ያለ ፍርሃት ነግደው የሚያተርፉባት፤ አዛውንቶች የሚጦሩባት፤ ህፃናት በደስታ የሚቧርቁባት፤ ገበሬው መሬት አልባ የማይሆንባት፤ ጋዜጠኛው ከሂሊናው ተስማምቶ ለሙያው ብቻ ታማኝ ሁኖ የሚኖርባት፤ ኪነ-ጥበብ የአደርባዮች መናኽሪያ ከመሆን ወጥታ አደርባዮችን ለመገሰፅ የምትችለበት፤ ዜጎቿ ያለ ፍርሃት የሚኖሩባት፤ ፍፁም ሠላም የሰፈነባት፤ በአጠቃላይ እግዚአብሄር አገሩ ኢትዮጵያ ነች ተብላ የምትታወቅ አገር ለመፈጠር ቆርጠን ተነስተናል። በዚህ መሠረትነት የጀመርነው ትግል ዕለት ዕለት እያማረበት፤ እየተጠናከረ እና እየጎለበተ እየሄደ ነው። ካሁን በኋላ ህወሃትን ከስልጣን ለማስወገድ ግዜውን የምንመርጠው እኛ እንጂ ማንም አይሆንም። ግዜው በደረሰ ግዜ አገራችንን እና ዜጎቿን ያዋረዱ በሙሉ ወየውላቸው። ከእኩይ አስተሳሰባቸው አንመለስም ያሉ በሙሉ የመጥፊያ ጉድጓዳቸውን እየማሱ እንደሆነ ስንነግራቸው ከክፉ አስተሳሰባቸው ለመመለስ አሁንም ቢሆን እንዳልዘገየ ልናስታውሳቸው እንወዳለን።
ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ !!

ድል የአላማ ጽናት እንጂ የመሳሪያ ጋጋታ ዉጤት አይደለም


pg7-logoጣሊያን ዋና ከተማ ሮም ዉስጥ ዋና ከተማዋን ከተለያዩ የጣሊያን ከተሞችና ጣሊያንን ከፓሪስ፤ከሙኒክ፤ከጄኔቫና ከቪዬና ጋር የሚያገናዉና በአመት ከ 150 ሚሊዮን በላይ መንገደኞችን የሚያስተናግድ አንድ ትልቅ የባቡር መስመር አለ። ይህ የባቡር መስመር የሚጠራዉ ሮማ ተርሚኒ እየተባለ ሲሆን የባቡር መስመሩ አድራሻ ደግሞ የአምስት መቶዎቹ አደባባይ በመባል ይታወቃል። ወደዘህ ትልቅ ባቡር መስመር ሲገባ አንድ እጅግ በጣም ትልቅ ሀዉልት ወለል ብሎ ይታያል፤ ይህም ሀዉልት የአምስት መቶዎቹ አደባባይ ወይም ፒያዛ ዴ ቺንኮቼንቶ በመባል የታወቃል። የፒያሳ ዴ ቺንኮቼንቶ መታሰቢያ ሀዉልት የተሰራዉ ወራሪዉ የጣሊያን ጦር አገራችንን ለመወረር ሲመጣ ዶጋሌ ላይ በራስ አሉላ ጦር የተገደሉትን አምስት መቶ የጣሊያን ወታደሮች ለማስታወስ ነዉ። በ1877 ዓም ዘመናዊ መሳሪያ ታጥቆ ጦርና ጎራዴ በታጠቀዉ የራስ አሉላ ጦር ዉርደት የተከናነበዉ የጣሊያን ወራሪ ሠራዊት ብድሩን ለመመለስ በ1888 ዓ.ም ብዛት ያለዉ ካባድ መሳሪያ፤ መድፍና መትረየስ ታጥቆ አድዋ ድረስ ቢመጣም በዳግማዊ ሚኒሊክ የተመራዉ ጀግናዉ የኢትዮጵያ ሠራዊት እንደገና ዉርደት አከናንቦት በጥቁር ህዝብ ታሪክ ዉስጥ ትዝታዉ ምንግዜም የማይደበዝዝ ድል አስመዝግቧል። የኢትዮጵያ ሠራዊት ዶጋሌና አድዋ ላይ እስካፍንጫዉ የታጠቀዉን የጣሊያን ወራሪ ጦር ደጋግሞ ያሸነፈዉ በመሳሪያ በልጦ ወይም የተሻለ የዉትድርና ችሎታ ስለነበረዉ ሳይሆን ከወራሪዉ ጦር የበለጠ ቆራጥነትና የአለማ ጽናት ሰለነበረዉ ነዉ።
በሃያኛዉ መቶ ክፍለ ዘመን የተደረጉ ሌሎች የነጻነት ትግሎችን ስንመለከት በወቅቱ የአየር ኃይል ያልነበራት ትንሿ አገር ቬትናም በባህር፤ በአየርና በየብስ ጦርነት የገጠማትን ትልቁን የአለማችን ሀይል አሜሪካንን አሸንፋ ነፃነቷን ያስከበረችዉ በመሳሪያ ጋጋታ ሳይሆን የዛፍ ላይ ቅጠልና የተቦጫጨቀ ጨርቅ በለበሱ ነገር ግን ከፍተኛ የአላማ ጽናት በነበራቸዉ ጀግኖች ልጆቿ አማካይነት ነዉ።
አለማችን ትልቅ የጦርነት አዉድማ ናት ቢባል አባባሉ እምብዛም ከእዉነት የራቀ አባባል አይደለም። በእርግጥም አለም የጦርነት መድረክ ናት። ወደድንም ጠላን ወይም ብናምንም ባናምንም ጦርነቶች ሁሉ የተካሄዱት የህዝብን ነፃነት በሚደፍሩ ኃይሎችና መብቴንና ነጻነቴን አትንኩ በሚሉ ኃይሎች መካከል ነዉ። የአለማችን ታሪክ ወለል አድርጎ እንደሚያሳየን ደግሞ ይዋል ይደር እንጂ ሁሉም ዘለቄታዊ ድሎች የተመዘገቡት የአላማ ጽናት ባላቸዉ መብቴንና ነጻነቴን አትንኩ በሚሉ ኃይሎች ነዉ እንጂ የመሳሪያ ጋጋታ በተሸከሙ ኃይሎች አይደለም። የመሳሪያ ጋጋታ የተሸከመና ብዛት ያለዉ ወታደር ያሰለፈ ነገር ግን ለምን እንደሚዋጋ የማያዉቅና የአላማ ጽናት የሌለዉ ሠራዊት ግዜያዊ የጦር የጦር ሜዳ ድል ለያገኝ ይችላል፤ ሆኖም ጦርነቱን አሸንፎና የህዝብን ነጻነት ቀምቶ መዝለቅ በፍጹም አይችልም።
የአለም ታሪክ በነጭ ወረቀት ላይ በጥቁር ቀለም ቁልጭ አድርጎ የጻፈዉ አንድ ግዙፍ ሀቅ ቢኖር እልፍ ታንክና እልፍ አዕላፋት መድፎች ቢታጠቁም አምባገነኖች ለግዜዉ እንደተቆጣ ነብር ያስፈራሉ እንጂ ህዝባዊ አለማና ጽናት ያለዉ ጦር ፊት ሲቆሙ ፀሐይ እንደገላመጠዉ በረዶ ሟሽሸዉ የሚጠፉ ደንባራ ፈረሶች ናቸዉ። ለዚህም ነዉ ህዝብ አምባገነኖችን የወረቀት ላይ ነብር እያለ የሚጠራቸዉ።
ዛሬ ዕድሜዉ 35 እና ከዚያም በላይ የሆነ ኢትዮጵያዊ ሁሉ የሚኒልክን ቤ/መንግስት ተቆጣጥረዉ የረገጡትን፤ የገደሉትንና መብቱንና ነጻነቱን ገፍፈዉ ያዋረዱትን ሁለት የወረቀት ላይ ነብሮች ያስታዉሳል የሚል ሙሉ እምነት አለን። ደርግ በ1967 ዓም “ያለ ምንም ደም እንከኗ ይዉደም” እያለ ወደ ሥልጣን ሲመጣ በፊዉዳሉ ስርዐት ጀርባዉ የጎበጠዉን ኢትዮጵያዊ ሁሉ ደስ አሸኝቶ ነበር። እየቆየ ሲሄድና የተደበቀ ትክክለኛ መልኩ አደባባይ ሲወጣ ግን ያንን “ያለ ምንም ደም” የሚለዉን መፈክሩን ረስቶ ኢትዮጵያን የደም ገንዳ ሲያደርጋት በኢትዮጵያ ህዝብ ተጠልቶ አይንህን ለአፈር ተባለ። በሩሲያ ሰራሽ ዘመናዊ የጦር መሳሪያዎች አስካፍንጫዉ የታጠቀዉና በቁጥሩና በወታደራዊ ብቃቱ አፍሪካ ዉስጥ ትልቁን ሠራዊት የገነባዉ ደርግ “እንደ ዉኃ የሚያጥለቀልቅ ኃይል አለኝ” እያለ ቢፎክርም እሱ እራሱ ተጥለቅልቆና በያለበት ተሸንፎ አገራችን ኢትዮጵያን ለዘረኛ አምባገነኖች ያስረከበዉ ለእግሩ ጫማ ለወገቡ መታጠቂያ በሌለዉ የገበሬ ጦር ተሸንፎ ነዉ። ደርግ እንደታጠቀዉ መሳሪያ ብዛት፤ እንዳደራጀዉ ወታደራዊ ብቃትና እንደ ወታደራዊ መሪዎቹ ችሎታ ቢሆን ኖሮ ደርግን እንኳን ተዋግቶ ለማሸነፍ በዉግያ ለመግጠምም የሚያስብ ኃይል በፍጹም አይነሳም ነበር፤ ነገር ግን ድል ምን ግዜም ቢሆን የመሳሪያ ጋጋታ ዉጤት ሳይሆን የራዕይ ጥራትና የአላማ ጽናት ዉጤት በመሆኑ በወቅቱ ይህንን የተገነዘቡ ኃይሎች ህብረትና አገር ዉስጥ የተቀሰቀሰዉ ህዝባዊ ቁጣ አንድ ላይ ሆነዉ ደርግን ጠራርገዉ የታሪክ ቆሻሻ ዉስጥ ሊጨምሩት ችለዋል።
ዛሬ ደርግን አሸንፈዉ ደርግ የተቀመጠበት ወንበር ላይ የተቀመጡት ዘረኞቹ የወያኔ መሪዎች የአገርን ኃብት ከመዝረፍ፤ የተቃወማቸዉን ከመግደልና የኢትዮጵያን አንድነት ከማፍረስ ዉጭ እንዴትና ለምን ደርግን የመሰለ ሠራዊት እንዳሸፉ የተገነዘቡ አይመስልም። ወያኔዎች ደርግ ከወደቀ ከ24 አመት በኋላ ዛሬም በየቀኑ ደርግን ቢኮንኑም ተቀምጠዉ አገር የሚገዙት ልበቢሱ ደርግ የተቀመጠበት ወንበር ላይ ነዉና የደርግ በሽታ ተጋብቶባቸዉ እነሱም እንደደርግ ልበቢሶች ሆነዋል።
ኢትዮጵያ በየዘመኑ እያደገና እየዘመነ የመጣ፤ ከተለያዩ የአገራችን ክፍሎች የተዉጣጣና ሞያን፤ ችሎታንና ወታደራዊ ሳይንስን አዳብሎ የታጠቀ ዘመናዊ የአገር መከላከያ ተቋም የነበራት አገር ነበረች። ዘረኞቹ የወያኔ መሪዎች አዲስ አበባን ሲቆጣጠሩ ይህንን ዘመናዊ የአገርና የወገን መመኪያ የሆነ ሠራዊት አፍርሰዉና በየበረሃዉ ለእናት አገሩ የተዋደቀዉን ሰራዊት ለማኝ አድርገዉት ነዉ እነሱ ወርቃማዉ ዘር ብለዉ በሚጠሩት ዘር የበላይነት ላይ የተመሰረተ የመከላከያ ተቋም የገነቡት። ወያኔ የገነባዉ የመከላከያ ተቋም ባለፉት ሃያ አራት አመታት ዉስጥ አዲስ አበባ፤ ኦጋዴን፤ ጋምቤላ፤ ደቡብ ኦሞና በተለያዩ የኦሮሚያ አካባቢዎች የወሰዳቸዉን ፀረ ህዝብና ፀረ አገር እርምጃዎች ስንመለከት ተቋሙ እዉነትም ለአገር ጥበቃ ሳይሆን የወያኔን የበላይነት ለማረጋገጥ የተቋቋመ ኃይል መሆኑን በቀላሉ መረዳት ይችላል።
ይህ ሙሉ በሙሉ በትግርኛ ተናጋሪዎች የሚታዘዘዉ መከላከያ ሠራዊት ጋምቤላና ኦሞ ሸለቆ ዉስጥ ገበሬዉ ከቀዬዉ ተፈናቅሎ መሬቱ ባዕዳን ሲቸበቸብ አፉን ዘግቶ እንዲመለከት አድርጓል። ይሄዉ ሠራዊት በ1997 ዓም በአግአዚ ነብሰ ገዳዮች እየተመራ የህዘብ ድምጽ ይከበር ያሉ ከ200 በላይ ሠላማዊ ዜጎችን በግፍ ጨፍጭፏል፤ ከዚህ በተጨማሪ የወያኔ መከላከያ ሠራዊት አጋዴንና ጋምቤላ ዉስጥ የዘር ማጥፋት ወንጀል ፈጽሟል አሁንም እየፈጸመ ነዉ። እዚህ ላይ የኢትዮጵያ ህዝብ አንድ ትኩረት ሰጥቶ ሊመለከተዉ የሚገባዉ ነገር አለ፤ እሱም ዘረኞቹ የወያኔ መሪዎች ልማታዊ ሠራዊት ብለዉ እያሞካሹና “የመከላከያ ኃይሎች ቀን” የሚል ስያሜ ሰጥተዉ በየአመቱ ማክበር የጀመሩት በዐል የሚያወድሰዉ ይህንኑ አንድነቱንና ነፃነቱን እጠብቃለሁ ብሎ ቃል ኪዳን የገባለትን ህዝብ ያለ ርህራሄ የሚጨፈጭፈዉን የወያኔ ሠራዊት ነዉ። በተለይ ወያኔ ባለፈዉ ሳምንት ባህር ዳር ዉስጥ ያለ የለሌ የመሳሪያ ጋጋታዉን አደባባይ አዉጥቶ ለህዝብ እያሳየ ባከበረዉ የመከላከያ ቀን በዐል ለህዝብ ማስተላለፍ የፈለገዉ መልዕክት ቢኖር “ይህንን እያያችሁ ከወያኔ ጋር በእሳት አትጫወቱ “ የሚል የሞኝ መልዕክት ነዉ።
ይህ ባህር ዳር ላይ የተላለፈዉ መልዕክት ለማን እንደሆነና በተለይ ባህር ዳር የመልዕክቱ ማስተላለፊያ ቦታ ሆና የተመረጠችበት ምክንያት ለማንም ኢትዮጵያዊ ግልፅ ይመስለናል። የዘረኞቹ የወያኔ መሪዎች መሰባሰቢያ የሆነዉ ህወሓት የተወለደዉም ሞቶ የሚቀበረዉም ሰሜን ኢትዮጵያ ዉስጥ መሆኑን እሱም ደጋፊዎቹም ካወቁ ቆይቷል። ዉቧና የጀግኖች መፍለቂያ የሆነችዉ ባህር ዳር ደግሞ ይህንን የወያኔን የቀብር ጉዞ ከጀመረች አመታት አስቆጥራለች። እንገዲህ ወያኔ በየቀኑ ከባድ መሳሪያና ስፍር ቁጥር የሌለዉ ወታደር ወደ ሰሜን ኢትዮጵያ የሚያጓጉዘዉ ከዚሁ ከማይቀርለት ዉድቀቱ የሚያድኑት እየመሰለዉ ነዉ። እዚህ ላይ አንድ ወያኔ በፍጹም ያልተረዳዉ ነገር ቢኖር ህወሓትን ከኢትዮጵያ ምድር ጠራርጎ የሚያጠፋዉና ግብዐተ መሬቱን የሚፈጽመዉ ይሄዉ ወያኔ በነጋ በጠባ ወደ ሰሜን ኢትዮጵያ የሚያጓጉዘዉ ሠራዊት መሆኑን አለመረዳቱ ነዉ። የወያኔ አይን ያወጣ ዘረኝነት በከፍተኛ ደረጃ ከተንጸባረቀባቸዉና በየቀኑ በዘረኝነት እሳት ከሚለበለቡ የህብረተሰብ ክፍሎች ዉስጥ አንዱና ዋነኛዉ የመከላከያ ሠራዊት ነዉ። ይህ ሰራዊት እንደ መሬት የሚረግጡትን የወያኔን አለቆቹን ትዕዛዝ ተቀብሎ ከታሰረበት የዘረኝነት እስር ቤት ነፃ ሊያወጡት በሚታገሉ የኢትዮጵያ ህዝብ የነጻነት ኃይሎች ላይ መሳሪያዉን ያዞራል ብሎ የሚያምን ኢትዮጵያዊ ያለ አይስለንም፤ በሌላ በኩል ደግሞ የወያኔን የመሳሪያ ጋጋታ አይቶ ለእናት አገሩ አንድነትና ለኢትዮጵያዉያን ወገኖቹ ነጻነት ህይወቱን ከመስጠት ወደ ኋላ የሚል ኢትዮጵያዊ ቢኖር እሱ ከወያኔ ጋር በጥቅም የተጋባ ከሃዲ መሆን አለበት። የኢትዮጵያ ህዝብ ምንግዜም ቢሆን በወሬ ቱማታና በመሳሪያ ጋጋታ ትጥቁን ፈትቶ አያዉቅም። በ1930ዎቹ ፋሺስት ጣሊያኖችንና በ1970ዎቹ ወታደራዊዉን ደርግ ተዋግቶ ያሸነፈዉ እነዚህ ኃይሎች የታጠቁትን መሳሪያ እየቀማ በተዋጋቸዉ ነጻነት የጠማዉ ኃይል ነዉ። የዛሬዎቹ የወያኔ ፋሺስቶች እጣም ጣሊያንና ደርግ ከገጠማቸዉ ሽንፈት የተለየ አይሆንም።
የአገራቸዉን የኢትዮጵያን ዳር ድንበር ከጠላት ለመከላከል የመከላከያ ሠራዊትን የተቀላቀሉ የኢትዮጵያ ልጆች “ዶሮን ሲያታልሏት በመጫኛ ጣሏት” የሚለዉን የአባቶቻቸዉ ምሳሌያዊ አባባል ምንነት በሚገባ የሚረዱ ይመስለናል። ስለሆነም ዘረኛዉ የወያኔ አገዛዝ በዘር ለይቶ እየረገጣቸዉ፤ እያዋረዳቸዉና ከሰዉ በታች አድርጎ እየተመለከታቸዉ ይህንን ቅጥ ያጣ በደል ለማረሳሳት የመከላከያ ቀን እያለ በሚያከብረዉን የይስሙላ በዐል እንድም የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት አባል ሊታለል አይገባም። ከአግአዚ ነብሰ ገዳዮች ዉጭ ያለዉ የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት እንደማንኛዉም የወያኔ እስረኛ እንደሆነ የህብረተሰብ ክፍል ነፃ መዉጣት የሚገባዉ ክፍል ነዉ። ይህ የህዝብ ወገን የሆነዉ የመከላከያ ሠራዊት እራሱን ብቻ ሳይሆን ኢትዮጵያዉያን ወንድሞቹንና እህቶቹን ጭምር ከወያኔ ዘረኝነት ነጻ ሚያወጣት አለበት። እስከቅርብ ግዜ ድረስ የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት አባላት ብዙም አማራጭ ስላልነበራቸዉ አንገታቸዉን ደፍተዉ የጠላታቸዉን የወያኔን ትዕዛዝ እየተቀበሉ ሲፈጽሙ ቆይተዋል፤ አሁን ግን አንገታቸዉን ቀና አድርገዉ የወያኔን አንገት የሚያሰደፉበት አመቺ ሁኔታ ተፈጥሮላቸዋል። ዛሬ ለእናት አገራቸዉ ነጻነት በህይወታቸዉ ቆርጠዉ ብረት ያነሱ የነጻነት አርበኞች የመከላከያ ሠራዊት የወያኔ አለቆቼን ትዕዛዝ ላለመቀበልም ሆነ ወይም የታጠቀዉን መሳሪያ ወደ ጠላቱ ወደ ወያኔ ማዞር የሚችልበትን አመቺ ሁኔታ ፈጥረዉለታል።
ዉድ የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት አባላት ሆይ ጨለማዉ ሊጠራ ሲል ይበልጥ ይጨልማልና ወያኔ ወደ ሰሜናዊዉ የአገራችን ክፍል የሚያጓጉዘዉ የመሳሪያ ጋጋታና የሠራዊት ብዛት በፍጹም ልትደናገጥ አይገባም። ወያኔን ካንተ በላይ በቅርብ የሚያዉቀዉ የለም፤ የወያኔ ኃይለኝነትና ትልቅ መስሎ መታየት አንተ በዉስጡ ስላለህበት ብቻ ነዉ። ስለዚህ ይህንን ፀረ ኢትዮጵያ ኃይል ለቅቀህ በያለህበት ላንተ፤ ለወገኖችህና ለእናት አገርህ ነፃነት መከበር ከቆረጡ ወገኖችህ ጋር በፍጥነት ተቀላቀል። ይህንን ማድረግ የማትችለዉ ደግሞ ወያኔ ከገዛ ወገኖችህ ጋር እንድትዋጋ ትዕዛዝ ሲሰጥህ የታጠከዉን መሳሪያ ወደ ወገኖችህ ሳይሆን ወደ ራሱ ወደ ወያኔ አዙር። ወያኔ ለትንሽ ግዜ የማይበገር መስሎ ሊታይ ይችል ይሆናል የማይቀረዉ የዘለቄታ ድል ግን ምን ግዜም የህዝብ ነዉ፤ የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት ደግሞ ትናንት አንደነበረ ሁሉ ዛሬም የኢትዮጵያ ህዝብ አለኝታ ነዉ።
ድል የህዝብ ነዉ!

አዋራጅ ሰልፎችና ድግሶች እንዲያበቁ ህወሓት ይወገድ!


pg7-logoድግሶችን፣ ወታደራዊ ሰልፎችንና ሀውልቶችን ማብዛት የአባገነኖች ሁሉ የጋራ ባህርይ ነው። ዘረኛውና ፋሽስቱ የህወሓት አገዛዝም በሕዝብ እየተጠላ፣ እያረጀና እየወላለቀ በሄደ መጠን በየተገኘው አጋጣሚ ሁሉ ደግሶ መብላት፤ ወታደራዊ ሰልፍና የመሣሪያ ጋጋታ ማሳየት እና በየመንደሩ ሀውልት መመረቅ ሙያው አድርጎት ቆይቷል።
የህወሓት ድግሶችና ፌሽታዎች የአገራችን ሀብት ከማሟጠጣቸውም በላይ የመንግሥት ሠራተኞችን፣ የአርሶ አደሮችንና የአነስተኛ ነጋዴዎችን ኪስ እያራቆቱ ናቸው። በአስር ሺዎች የሚቆጠሩ የኦሮሞ ተወላጆች በእስር ቤቶች እየማቀቁ በሚገኙበት ሁኔታ፤ በመቶ ሺዎች የሚገመቱ የአማራ አርሶአደሮች ተፈናቅለው እያለ፤ በጋምቤላና በኦጋዴን ወገኖቻችን ላይ ዘግናኝ የጅምላ ጭፍጨፋዎች እየተደረጉ፤ በአፋር፣ በሲዳማ፣ በቦረና፣ በወልቃይት እና በመላው ኢትዮጵያ ግጭቶች በበዙበት፤ ሕዝብ እያለቀሰ ባለበት በአሁኑ ሰዓት “የብሔር፣ ብሔረሰቦች መብት ተከበረ” እያሉ እነዚህኑ በደል እየደረሰባቸው ያሉ ዜጎችን ማስጨፈር እና ለእነዚህ ጭፈራዎች በርካታ ሚሊዮኖች ብር ማውጣት በእጅጉ ያስቆጫል። እነዚህ ጭፈራዎች ለህወሓት ሰዎች የገቢ ምንጮች መሆናቸው ጥርጥር የለውም፤ ለድሀው ኢትዮጵያዊ ግን መራቆቻዎች ናቸው። ከዚህም አልፎ በዘረኝነት እየተበደለ ያለ ሕዝብ ስለእኩልነት ዝፈን ማለት ክብረ ነክ ተግባር ነው። ዘንድሮ በአሶሳ የተደረገው አገር አቀፍ ድግስ ካለቀ ጥቂት ወራት በኋላ አገራችን በሌላ ዙር የህወሓቶች ድግስ ተወጥራለች።
ሰሞኑን በባህር ዳር በተደረገው የጦር ሠራዊት ሰልፍ እና ሰልፉን ተከትሎ በነበረው የድግሶች ግርግር ከሁሉም በላይ የተሰደበውና የተዋረደው የሠራዊቱ አባል ነው። አዛዦቹ መቶ በመቶ የህወሓት አባላት የሆኑበትን ሠራዊት “የኢትዮጵያ መከላከያ” ተብሎ መጠራቱ ራሱ የሚያሳፍረው ኢትዮጵያዊ ወኔ በልባቸው ውስጥ እየተንቀለቀለና እልህ እየተናነቃቸው ያሉ የሠራዊቱን አባላት ነው። የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት እንዴት የኢትዮጵያ ጠላቶች በሆኑ የህወሓት ካድሬዎች ይመራል? እንዴት የአስር አለቃ እንኳን ሊሆን የማይገባው የህወሓት ካድሬ “ጄኔራል” ተብሎ ኢትዮጵያዊያን ወታደሮችን እንደ ሎሌው ያዛል? እንዴት አንድ የህወሓት ሎሌ ሹመት ተሰጥቶት እየፏለለ በልምድ፣ በትምህርትና በእውቀት የሚበልጠውን ኢትዮጵያዊ ተንቆ ይዋረዳል? ይህ ቁጭትና እልህ ሠራዊቱ የዘረኛውን ህወሓት ሰልፍ አድማቂ መሆኑ የሚያከትምበት ጊዜ ይበልጥ እንዲናፍቅ የሚደረገው ነው። አልያማ ሰልፍ ያሳመረ ሠራዊት ሁሉ አሸናፊ እንዳልሆነ የታወቀ ነው። በሰልፍ ብዛትና በመሣሪያ ትዕይንት ማሸነፍ ቢቻል ኖሮ የትም አገር አምባገነኖች ባልወደቁም፤ ህወሓት ራሱን ስልጣን ላይ ባልወጣም ነበር።
የህወሓት ምሥረታ 40ኛ ዓመት ድግስም ሌላው የታሪክና የሀብት ውድመት የሚያስከትል ክስተት ነው። የካቲት 11 ቀን 1967፣ ጥቂት ኢትዮጵያዊያን እናታቸውን ኢትዮጵያን ለመግደል ያሴሩበት እና ልጆች በእናታቸው ላይ ቢላዋ የሳሉበት ዕለት በመሆኑ በሀዘንና በሱባኤ እንጂ በድግስና በጭፈራ የሚታሰብ ዕለት አይደለም። ሲነሳ ምንም ይሁን ምን ዛሬ በደረስንበት ሁኔታ ሲገመገም፣ ኢትዮጵያ በታሪኳ ውስጥ ህወሓትን የመሰለ መሠሪና አድርባይ ድርጅት ገጥሟት አያውቅም። እነሆ ዘንድሮም ይኸው አድርባይ ድርጅት የመሪዎቹን የሀብትና ዝና ረሀብ ለማስታገስ ሲል ያልነበረ ታሪክ እየፈጠረ በድግስ ስም ከድሀው ገንዘብ እየሰበሰበ ለሀብታም የህወሓት አባላትና ደጋፊዎች ያሸጋግራል። የድግሶቹ ሁሉ አዘጋጆች፣ እቃ አቅራቢዎችና ተጠቃሚዎች ራሳቸው የህወሓት መሪዎችና አሽቃባጮቻቸው ሲሆኑ ከፋዩ ግን የኢትዮጵያ ሕዝብ ነው። በህወሓት ድግስ የሚባክነው የሕዝብ ሀብት ስንት ሆስፒታል ይገነባ እንደነበር ስናስብ እና ይህ ሀብት በተገቢው ቦታ ውሎ ቢሆን ኖሮ ዛሬ ስም ብቻ የያዙ ዩንቨርስቲዎቻችንን ትምህርት መቅሰሚያ ማድረግ እንችል እንደነበር ስናሰላ ሀዘናችን ጥልቅ ነው። ህወሓት ለልጅ ልጆቻችን የሚተርፍ ዕዳ እየቆለለ ዳንኪራ ሲረግጥና ሲያስረግጥ ማየትና መስማት ህሊና ሊሸከመው ከሚችል በላይ ነው።
አርበኞች ግንቦት 7፡ የአንድነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ በህወሓት ወታደራዊ ሰልፍ እና የመሣሪያዎች ትዕይንት የሚረበሽ ድርጅት አይደለም። ይልቁንም በሰልፉ ጨኸት የታፈነው የኢትዮጵያዊ ወታደር ጩኸት ይሰማዋል። ኢትዮጵያዊ ወታደር በአዛዦቹ ላይ ጥርሱን ነክሶ፣ ቂም አርግዞ ሰልፋቸውን እንደሚሰለፍ አርበኞች ግንቦት 7 ያውቃል። አርበኞች ግንቦት 7፣ የሠራዊቱ አባላት ውስጥ ውስጡን እየተሰቃዩ የታዘዙትን መፈፀማቸው መብቃት አለበት ይላል፤ ወይ ተቀላቀሉን፣ አሊያም እውስጡ ሆናችሁ ሥርዓቱን የማዳከም ሥራዎችን ሥሩ። በእናንተ ውርደት የዘራፊዎች፣ ሙሰኖች፣ ጎጠኞችና ዘረኞች ደረት አብጦ መታየት የለበትም።
አርበኞች ግንቦት 7፣ የዘንድሮው የህወሓት 40ኛ ዓመት በዓል የጨረሻው በዓል እንዲሆን፤ ከርሞም ተመሳሳይ አዋራጅ በዓል እንዳናከብር፤ ሠራዊቱ በዘራፊዎች ታዞ የሚሰለፍበት ውርደት እንዲያበቃ ተባብረን ህወሓትን እንቅበር ይላል።
ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ!

Friday 20 February 2015

የ2007ቱን ሀገራዊ ምርጫ ሂደት እና ከምርጫዉ ዉጭ ያሉ አዋጭ አማራጮችን በተመለከተ የአርበኞች ግንቦት 7: የአንድነትና ዲሞክራሲንቅናቄ የአቋም መግለጫ


pg7-headerአርበኞች ግንቦት 7: የአንድነትና ዲሞክራሲ ንቅናቄ፣ የኢትዮጵያ ሕዝብ በሰላማዊ፣ ተዓማኒና ፍትሀዊ በሆነ ምርጫ የማይፈልጋቸውን መሪዎች መሻር፤ የሚፈልጋቸውን ደግሞ መሾም የሚያስችሉትን መሠረቶች ለመጣል የሚታገል ንቅናቄ ነው። እንደሚታወቀው የሕዝብ እውነተኛ ፍላጎት የሚገለጽበት እውነተኛ ምርጫ እንዲኖር ገለልተኛና ቀልጣፋ የፍትህ ሥርዓት፣ የጦርና የፓሊስ ሠራዊት ሊኖሩ ይገባል። ነፃ የሚዲያ ተቋማትና በነፃነት የሚንቀሳቀሱ የሲቪክ ማኅበራት መኖርም መታለፍ የሌለባቸው አቢይ ጉዳዮች ናቸው። አማራጭ ፓሊሲዎችን ማቅረብ የሚችሉ በነፃነት የሚንቀሳቀሱ የፓለቲካ ፓርቲዎች ከሌሉም አማራጮች የሉምና ምርጫ ትርጉም የለውም። ይህ ሁሉ ቢሟላ እንኳን ምርጫውን የሚያስፈጽመው አካል ገለልተኛ፣ ሀቀኛና ተዓማኒ ካልሆነ የሚደረገው ምርጫ የመራጩን ሕዝብ ፍላጎት የሚያንፀባርቅ ሊሆን አይችልም።
ከላይ የተዘረዘሩትን የምርጫ እሴቶች ሙሉ በሙሉ ባይሆንም እንኳን የተወሰኑትን በመጠኑም ቢሆን ያካተተ ምርጫ እንዲኖር መጣርና በሂደት የምርጫውን አፈፃፀም ማሻሻል ይቻል ይሆናል በሚል እምነት የዲሞክራሲ ኃይሎች በህወሓት የሴራ ምርጫዎች ሲሳተፉ ቆይተዋል። ሆኖም በህወሓትና በእውነተኛ ምርጫ መካከል ያለው ተቃርኖ እያደር እየሰፋ ሲሄድ እንጂ ሲጠብ አልታየም። በህወሓት ሙሉ ቁጥጥር ስር በሚካሄድ ምርጫ ኢትዮጵያን የሚጠቅም ለውጥ ሊመጣ ይችላል የሚለው እምነት ለአርበኞች ግንቦት 7 ፈጽሞ የተሟጠጠው ከምርጫ 97 ማግስት ጀምሮ ነው። በግንቦት 7 ቀን 1997 ዓም የኢትዮጵያ ሕዝብ በታላቅ የለውጥ ተስፋ የሰጠው ድምጽ በህወሓት የተዘረፈው ከላይ የተዘረዘሩት ተቋማት ያልነበሩ በመሆናቸው፤ ስለዚህም ከምርጫ በፊት ተቋማቱን መገንባት፤ ተቋማቱን ለመገንባት ደግሞ ህወሓትን ከስልጣን ማስወገድ ይገባል ብሎ በማመኑ ነው አርበኞች ግንቦት 7 በሁለገብ የትግል ስልት በመንቀሳቀስ ላይ የሚገኘው።
ያም ሆኖ ግን በምርጫ ላይ ያላቸው ተስፋ ፈጽሞ ያልተሟጠጠ ፓርቲዎችን በማክበርና ሥራቸውንም አስቸጋሪ ላለማድረግ ሲባል ከምርጫ 97 ወዲህ የነበሩ ብሄራዊም ሆነ ክልላዊ ምርጫዎችን አስመልክቶ የኢትዮጵያ ሕዝብ ከምርጫ ዉጭ ያሉ ሌሎች አማራጮችን ብቻ እንዲመለከት አርበኞች ግንቦት 7 ጥሪ አድርጎ አያውቅም ነበር። አሁን ግን የአገራችን ኢትዮጵያ የፓለቲካ ሁኔታዎች ይህንን የቆየ አቋም በሚያስቀይር መንገድ፤ የአገራችንን የወደፊት ዕድል ብቻ ሳይሆን ባጠቃላይ ያካባቢውን ሰላም በሚጎዳ መልኩ ተቀይሯል። የሰሞኑ የወያኔ እርምጃዎች ትንሽ ተስፋ ያደርግ የነበረውን የዴሞክራሲ ወገንተኛ ተስፋም እምሽክ አድርጎ በልቶታል:: እየተቃረበ ያለው ዓይነት የፌዝ ምርጫ ወያኔ እንደ እንጄራ የራበውን የተቀባይነት እጦት ለአጭር ጊዜ ያስታግስለት ይሆናል እንጂ የሀገሪቱን እያደር እየተወሳሰበ የመጣ ችግር ለጊዜውም እንኳን የሚያስታግስ አይሆንም፤ ይልቁንም ጊዜው በገፋ ቁጥር ችግሩ መቋጠሪያ የጠፋው እየሆነ ይሄዳል::
የሁኔታውን አሳሳቢነት ከግምት ውስጥ በማስገባት የአርበኞች ግንቦት 7: የአንድነትና ለዲሞክራሲ ንቅናቄ አመራር የወቅቱን የአገራችን የፓለቲካ ሁኔታ በጥንቃቄ መርምሮ የሚከተሉት ግንዛቤዎች ላይ ደርሷል።
1. ህወሓት ብዙዎች እትዮጵያዊያን የተሰውላቸውን አንድነት ፓርቲንና መኢአድን በመበተን የድርጅቶቹን ስምና ንብረት ለአገልጋዮቹ መስጠቱ፤ ከዚህ በፊት ሲያደርግ እንደነበረው የመራጭን ድምጽ መስረቅ ሳይበቃው የምርጫ ተወዳዳሪንም መዝረፍ መጀመሩን አመላካች ነው። ይህ ተግባር ህወሓት የምርጫ ውጤትን ብቻ ሳይሆን ተወዳዳሪዎችንም እሱ ራሱ ለመምረጥ መወሰኑን ያሳያል፤ ከዚህ በተጨማሪ የሴራ ምርጫውን ከጅምሩ ጀምሮ አስቀድሞ እስከተወሰነለት መዳረሻው ድረስ ለምንም ዓይነት ያልተጠበቀ አጋጣሚ (በምርጫው ወቅት የሚደረጉትን ክርክር ተብዬዎች ጨምሮ) እድል ላለመስጠት ወስኖ እየተንቀሳቀሰ መሆኑን በግልጽ ያሳያል፤
2. ይህ እኩይ ውሳኔ በምርጫ ቦርድ ፊርማና አንደበት ቢነገርም ምንጩ የህወሓት ፓሊት ቢሮ መሆኑን የሚከተሉት ተግባራት ይጠቁማሉ፤
2.1. በምርጫ ቦርድ በኩል እንዲገለጽ የተወሰነው እርምጃ ለማስመሰል ያክልም ቢሆን የህጋዊነት ሽፋን እንዲኖረው አለመደረጉ ውሳኔው ፍጹም እብሪተኛ በሆነ አካል መወሰኑን ያመለክታል። እንዲህ ዓይነቱ እብሪተኛ አካል ደግሞ የህወሓት ፓሊት ቢሮ ነው። ውሳኔውን ለማስፈፀም የነበረው ጥድፊያም ይህንኑ ያጠናክራል።
2.2. ለማስመሰያ ያክል እንኳን ምንም አይነት የፍርድ ቤት ትዕዛዝ ሳይኖር ፓሊስ የአንድነትና የመኢአድ ቢሮዎችን መውረሩ፤ ህወሓት አንድነትንና መኢአድን አጥፍቶ የድርጅቶቹን ስሞችና ንብረቶች ለሚፈልጋቸው ሰዎች ሰጥቶ በአስቸኳይ ለምርጫ ድራማው በፊት መስመር ሊያሰልፋቸው መወሰኑን አመላካች ነው። እንዲህ ዓይነት ከባድ ውሳኔ የሚሰጠው ደግሞ የህወሓት ፓሊት ቢሮ ብቻ ነው።
2.3. ወደ ፈቃድ መንጠቅ ከመደረሱ በፊትም በሰማያዊ ፓርቲ፣ በአንድነትና በመኢአድ አባላት የደረሰው አረመኔያዊ ድብደባ፤ ንቁ የፓለቲካ ተሳትፎ የሚያደርጉ ዜጎች ላይ የሚደርሰው እስር፣ መሰወርና እና ባልታወቁ ሰዎች ተገድሎ መገኘት መብዛት እነዚህን አገራዊ ፓርቲዎች የመበተን የፓለቲካ ውሳኔ መሰጠቱን አመላካቾች ናቸው።
3. ለጊዜው የፈቃድ ነጠቃና የንብረት ዘረፋ የተፈፀመው በአንድነትና በመኢአድ ላይ ቢሆንም በሰማያዊ ፓርቲ ላይ በየእለቱ እየጠነከረ የመጣው የአፈና እርምጃም በተመሳሳይ ፓርቲውን ወደማገድ አለዚያም ፈጽሞ መንቀሳቀስ ወደማይችልበት ደረጃ ሊያደርሰው ይችላል የሚል እምነት አሳድሯል። ሌሎች ፓርቲዎችም ከዚህ ህወሓት ካሰመረው የውሸት ጫወታ መስመር የመውጣት ዝንባሌ ቢያሳዩ ተመሳሳይ እርምጃ አይቀርላቸውም።
4. የህወሓት የወቅቱ የጥፋት ዒላማ ያነጣጠረው አንፃራዊ በሆነ መንገድ የተሻለ መዋቅርና ማኅበራዊ መሠረት ባላቸው እና በአገራዊ አጀንዳዎቻቸው በሚታወቁ ፓርቲዎች ላይ መሆኑ፤ የወቅቱ የጥፋት ዘመቻ የኢትዮጵያ አንድነትን የማዳከምና ከፋፍሎ የመግዛት የህወሓት ትልቁ አጀንዳ አካል መሆኑን ያሳያል።
5. እራሱን በዘር ያደራጀዉና ኢትዮጰያ ዉስጥ ያለዉ ፖለቲካዊና ማኅበራዊ አደረጃጀት ከዚሁ እሱ ከተደራጀበት የዘር አደረጃጀት ዉጭ እንዲሆን በፍጹም የማይፈቅደዉ የወያኔ አገዛዝ፤ መጣፊያው ሲያጥረውና ወደ ማይቀረው ውድቀቱ ሲያመራ፤ እኔ ከሞትኩ ሰርዶ አይብቀል እንዳለችው አህያ አገራችን ኢትዮጵያን በቀላሉ ወደማትወጣዉ የዘዉግ ግጭት ዉስጥ አስገብቶ ዘመናት ያስቆጠረዉ አንድነቷ እንዲፈረስ በትጋት እየሠራ መሆኑን ያሳያል።
6. ከመለስ ዜናዊ ሞት ወዲህ ህወሓት ከሁሉን ጠቅላይ (totalitarian) አገዛዝ ወደ ፋሽስታዊ ቡድንነት ያሽቆለቆለ መሆኑን አርበኞች ግንቦት 7 ተገንዝቧል። ህወሓት ዘረኛ፣ ጠቅላይና ፈላጭ ቆራጭ ጨቌኝ በመሆኑ ፋሽስት ብለነዋል። ሆኖም በታሪክ የሚታወቁ ፋሺስታዊ አገዛዞች ከፍተኛ ብሄራዊ ስሜት የነበራቸው ሲሆን የህወሓት ፋሽስታዊ አገዛዝ ግን ብሔራው ስሜት አልባ መሆኑ ልዩ እና የበለጠ አደገኛ ያደርገዋል። ይህ ፋሽስታዊ ቡድን የህወሓት መሪዎችንና ጥቂት ሌሎች አጫፋሪዎቻቸውን የያዘ ለጊዜው አስተባባሪ መሪ የሌለው ሆኖም ግን የጦር ሠራዊትን፣ የስለላ መዋቅሩንና ፓሊስን ተቆጣጥሮ በአሁኑ ሰዓት ኢትዮጵያን እየገዛ ያለው ይህ አስኳል የለሽ ፋሽስታዊ ቡድን መሆኑ እጅግ አሳሳቢ ጉዳይ መሆኑን አርበኞች ግንቦት 7 ተገንዝቧል። ይህ ፋሽስታዊ ቡድን ተደላድሎ መሪ እንዲፈጥር ከተፈቀደለት አገራችንን የከፋ መከራ ውስጥ ሊከታት እንደሚችል ግንዛቤ ተወስዷል።
ከላይ በአጭሩ ከተራ ቁጥ 1 እስከ 6 የተዘረዘሩትን በማገናዘብ በግንቦት 2007 ሊደረግ የታቀደውን አምስተኛው ዙር ሀገር አቀፍ የሴራ ምርጫን በተመለከተ የአርበኞች ግንቦት 7 አመራር ውሳኔዎችን አስተላልፎ ከዚህ የሚከተሉት ጥሪዎችን ለኢትዮጵያ ሕዝብ አቅርቧል።
1. በምርጫ 2007 መሳተፍ ለዲሞክራሲያዊ ለውጥ ሁኔታዎችን ከማመቻቸት ይልቅ ፋሽስታዊውን ቡድን የሚያጠናክርና የኢትዮጵያን ሕዝብ የወደፊት ዕድል የሚገድል በመሆኑ፣ ለፍትህ፣ ለነፃነት፤ ለዲሞክራሲና ለአገር አንድነት ግድ ያላቸው ወገኖች ሁሉ ከአሁኑ ከዚህ የይስሙላ ምርጫ ዉጭ ዓይኖቻቸውንና ሙሉ ጉልበታቸዉን በሌሎች የኢትዮጵያን ሕዝብ ነፃነት በሚያፋጥኑ አማራጮች ላይ እንዲያሳርፉ ጥሪ ያደርጋል። አርበኞች ግንቦት 7 የኢትዮጵያ ሕዝብ ከዚህ ዓይን ያወጣ የሴራ ምርጫ ይልቅ መብቱን፤ ነፃነቱንና እኩልነቱን በሚያፋጥኑለት በሕዝባዊ እምቢተኝነትና በሕዝባዊ አመፅ የትግል አመራጮች ላይ እንዲሳትፍ ለመላው ያገሪቱ ሕዝብ ጥሪ ያስተላልፋል። ህወሓት ማኅበረሰባችንን ለመከፋፈልና ለማባላት የሚያደርገውን እኩይ ሴራ በጋራ እንድናከሽፈው ወገናዊ ጥሪ ያስተላልፋል፤ “አንከፋፈልም፤ ተከፋፍለንም አንጠቃም“ እንበል ይላል::
2. ህወሓትን ማስወገድ የሚቻለው በሕዝባዊ እምቢተኝነትና በሕዝባዊ አመጽ በመሆኑ፤ ከሁለቱ አንዱንም አለመያዝ ሌላ ሰው ታግሎ ነፃነቴን ያቀዳጀኝ እንደማለት የሚቆጠር በመሆኑ፤ እያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ በአፋጣኝ ከእነዚህ ሁለት የትግል ዘርፎች ዉስጥ የተሻለ አስተዋጽኦ አበረክታለሁ በሚለው የትግል ዘርፍ ውስጥ ተሳትፎ እንዲያደርግ ጥሪ ያቀርባል።
3. አርበኞች ግንቦት 7፣ በሁለቱም የትግል ዘርፎች ድርጅታዊ መዋቅሩን እያሰፋና ከሌሎች ድርጅቶች ጋር በመተባበር በሕዝባዊ እምቢተኝነትና በሕዝባዊ አመጽ ህወሓትን ከስልጣን ለማስወገድ አቅዶ በመንቀሳቀስ ላይ የሚገኝ በመሆኑ ኢትዮጵያዊያን በስፋት እንዲቀላቀሉት፤ በኅብረት እንድንቆም እና የህወሓትን ውድቀትና የኢትዮጵያን ትንሳኤ እንድናፋጥን ጥሪ ያደርጋል::
4. ያለንን አቅም በሙሉ ህወሓትን በማስወገድ ላይ ካዋልነው አንድ ጠንክር ያለ ሕዝባዊ አመጽ አገዛዙን ሊያፍረክርክው የሚችል በመሆኑ፤ በአንድ ወይም በሌላ መንገድ ከምርጫ ጋር ለተያያዙ ሥራዎች ሊውል ታስቦ የነበረው የሰው ኃይል፣ ጊዜ፣ ገንዘብና እውቀት ለሕዝባዊ አብዮት መቀስቀሻነት እንዲውል ጥሪ ያደርጋል።
5. በውጭ አገራት የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ወገኖቻችንም በ2007 ምርጫ ላይ ጊዜና ንብረት ከማባከን ይልቅ በአንድ ልብ በኢትዮጵያ ውስጥ ለሕዝባዊ አብዮት መቀስቀስ የበኩላቸውን አስተዋጽኦ እንዲያደርጉ ጥሪ ያደርጋል። ከሁሉም ዴሞክራሲያዊ ኃይሎች የተውጣጣ አካል የዚህን ጥሪ ተፈፃሚነት እንዲከታተል ቢደረግ ይበልጥ ውጤታማ ይሆናል ብሎ ያምናል።
ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ!
አርበኞች ግንቦት 7: የአንድነትና ዲሞክራሲ ንቅናቄ
ሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ

Thursday 12 February 2015

የትግራይ ሕዝብንና የኢትዮጵያ ፓሊስን በኢትዮጵያዊያን ለማስጠላት የሚደረገው ጥረት ከሽፏል!


ህወሓት ንፁሀንን ለመደብደብ የሚያበቃ በቂ ክፋት ያለው ልዩ ጦር ሲያሰለጥን ቆይቷል። ይህን ልዩ ጦር የፓሊስን መለያ እያለበሰ ነውረኛ ሥራዎችን እንዲሠራ በማድረግ በአንድ በኩል ንፁሀንን የመጉዳት በሌላ በኩል ደግሞ ፓሊስን በሕዝብ የማስጠላት መንታ ግቦችን ለማሳካት ተጠቅሞበታል። ይህ ልዩ ጦር በአለፉት ጥቂት ሳምንታት ባዶ እጃቸው ለተቃውሞ በወጡ ነብሰ ጡር ሴቶች ላይ ሳይቀር ባሳየው ጭካኔ፣ በሰማያዊ እና በአንድነት ፓርቲ አባላትና ደጋፊዎች ላይ ባደረሰው ድብደባ መጠን እና ባካሄደው የግለሰብ ንብረቶች ዝርፊያ የሥርዓቱ ባህርይ ፈጽሞ ከሰውኛ ተፈጥሮ እየወጣ እንደሆነ አመላካች ነው። በእነዚህ ድብደባዎች ወቅት በትግራይ ተወላጆች ላይ የተለየ ትኩረት በማድረግ ከፍተኛ ጉዳት እንዲደርስባቸው ተደርጓል። በትግራይ ተወላጆች ላይ የተለየ ትኩረት የተደረገው በደብዳቢዎቹ የግል ውሳኔ ሳይሆን ከበላዮቻቸው በተሰጠ ትዕዛዝ ነው ብሎ አርበኞች ግንቦት 7 ለአንድነትና ዲሞክራሲ ንቅናቄ ያምናል።
በአርበኞች ግንቦት 7: እምነት መሠረት የፓሊስ ከፍተኛ አዛዦች ህወሓቶች ቢሆኑም አብዛኛው የሠራዊቱ አባል በህወሓት ዘረኛና ፋሽስታዊ አገዛዝ የተማረረ፤ የሥርዓቱ መለወጥ የሚፈልግና ሥርዓቱን ለመለወጥ የሚደረገውን ትግል የሚደግፍ ኃይል ነው። ስለሆነም ህወሓት የተለየ ጦር አሰልጥኖ የፓሊስ ልብስ በማልበስ ነውረኛ ወንጀል በማሠራት ፓሊስን ለማስጠላት የሚያደርገው ሴራ ሊጋለጥ ይገባል ብሎ ያምናል። የፓሊስ ሠራዊት አባላትም በስማቸውና በደንብ ልብሳቸው የሚደረገውን ደባ ባገኙት አጋጣሚ ሁሉ እንዲያጋልጡ አርበኞች ግንቦት 7 ያሳስባል።
ህወሓት እንደሚያስበው እና የኢትዮጵያም ሕዝብ እውነት አድርጎ እንዲቀበለው እንደሚፈልገው የትግራይ ሕዝብ በጅምላ የህወሓት አፍቃሪና ደጋፊ አይደለም። እንዲያውም በተፃፃሪው ህወሓት ከትግራይ ተወላጆች ልብ እየተነቀነ ነው። የትግራይ ሕዝብ ዲሞክራሲያዊ ንቅናቄ (ትሕዴን/ደምህት) ከትግራይ የበቀለ፤ ህወሓትን በአመጽ ለመፋለም የቆረጠ ኃይል ነው። አርበኞች ግንቦት 7 በትግራይ ውስጥ ብዙ ደጋፊዎች ያሉት መሆኑ የምናውቀው ሀቅ ነው። አረና ትግራይ ህወሓትን በሰላማዊ መንገድ ለመታገል የተነሳ ተሰሚነቱን በከፍተኛ ደረጃ እያደገ የመጣ እና አቶ አብርሀ ደስታን የመሰለ ወጣት ኢትዮጵያዊ የፓለቲካ መሪ ያወጣ ድርጅት ነው። ህወሓት አንድነት ፓርቲ ላይ የመረረ አቋም ከወሰደባቸው ምክንያቶች አንዱ በትግራይ ውስጥ ያለው ተቀባይነት በከፍተኛ ፍጥነት እየጨመረ መምጣቱ ነው። ህወሓት የትግራይን ሕዝብ ከተቀረው የኢትዮጵያ ሕዝብ በጅምላ ለማጣላት የሚያደርገው ጥረት ማክሸፍ ይኖርብናል ብሎ አርበኞች ግንቦት 7 ያምናል፤ ለዚህም ተግቶ ይሠራል። አርበኞች ግንቦት 7 ከትግራይ የዲሞክራሲ ኃይሎች ጋር በመተባበር ፀረ ህወሓት ትግል በትግራይ ውስጥ መቀጣጠል ይኖርበታል ብሎ ያምናል። በዚህም መሠረት ትግራይ የህወሓት መቀበሪያ የመሆኗ ጊዜ ሩቅ አይደለም።
በዘንድሮው የ2007 የሴራ ምርጫ አማካይነት ተድበስብሰው የመጡ እነዚህ ሁለት ክፋቶች ማለትም ፓሊስን በሕዝብ ማስጠላት እና የትግራይ ተወላጅ የሆኑ የዲሞክራሲ ወገንተኞችን ለይቶ ማጥቃት ከበስተጀርባቸው ያዘሉት እኩይ ዓላማ መጋለጡ መንገዳችን ያጠራልናል ብሎ አርበኞች ግንቦት 7 በጽኑ ያምናል። በአንድነትና በመኢአድ የተፈፀው የድርጅትና የንብረት ዘረፋም የዚሁ ፕሮጀክት አካል መሆኝ ግልጽ ነው፤ ነገ ተመሳሳይ ነገር በሰማያዊ ፓርቲም ላይ ይፈጽም ይሆናል።
በመሆኑ ከ2007 የሴራ ምርጫ ትሩፋቶች በትግራይ ሕዝብና በፓሊስ ሠራዊት ጀርባ የሚደረገው ደባ መጋለጡ ነው። ይህ ድል ጽኑ መሠረት እንዲይዝ ህወሓትንና የትግራይን ሕዝብ የመነጠል እና ፓሊስ የሕዝብ አጋር መሆኑን የማረጋገጥ ሥራዎችን አጠናክረን መሥራት እንዳለብን አርበኞች ግንቦት 7 ያሳስባል።
ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ !

Wednesday 11 February 2015

ለወያኔ ዉንብድና መልሱ ህዝባዊ እምቢተኝነትና ህዝባዊ አመጽ ነዉ!


pg7-logoዘረኞቹ የወያኔ መሪዎ የኢትዮጵያን በትረ ስልጣን ጨብጠዉ በኖሩባቸዉ ባለፉት ሃያ አራት አመታት የአገራችን የኢትዮጵያን የፖለቲካ መድረክ ከዚህ ቀደም ታይቶ በማይታወቅ መልኩ እጅግ በጣም ከዘቀጠና ከረከሰ የወያኔ ድራማ ዉጭ ሌላ ምንም ነገር የማይታይበት አለባሌ መድረክ አድረገዉት ቆይተዋል አሁንም እያደረጉት ነዉ። አንድ ቋንቋ የሚናገሩትና ተመሳሳይ አመለካከት ያላቸዉ የወያኔ መሪዎች ኢህአዴግ የሚባል አጋሰስ የሽፋን ድርጅት ፈጥረዉ በኢትዮጵያ ህዝብ ሰብዓዊ መብትና ነጻነትና ላይ ተነግሮም ተጽፎም የማያልቅ ግዙፍ ግፍና በደል ፈጽመዋል። ህጻን፤አዛዉንት፤ ወንድና ሴት ሳይለዩ መብቴን አትንኩ ያለቸዉን ኢትዮጵያዊ ሁሉ ያለምንም ርህራሄ በጥይት ጨፍጭፈዋል። ሴቶች እሀቶቻችንን እጅና እግራቸዉን አስረዉ ጡታቸዉን በመቆንጠጫ እየቆነጠጡ በሴትነታቸዉ ላይ የዉርደት ተግባር ፈጽመዋል። ወንዶች ወንድሞቻችንን ደግሞ ዉስጥ እግራቸዉን ገልብጠዉ እየገረፉ ጥፍራቸዉን አይናቸዉ እያየ በጉጠት እየሳቡ ነቅለዋል። ባጠቃላይ የወያኔ ዘረኞች በዛሬዉ ዘመን አንኳን ወገን በወገኑ ላይ የዉጭ ጠላትም በህዝብ ላይ የማይፈጽመዉ በደል በኢትዮጵያ ህዝብ ላይ ፍጽመዋል።
ወያኔ ስልጣን እንደያዘ “አባይ ትግራይ” ወይም “ታላቋ ትግራይ” የሚለዉን ህልሙን ለማሳካት ወልቃይት ጠገዴን ከጎንደር ቆርሶ ከትግራይ ጋር ቀላቅሏል። ስልጣን ይዞ ከተደላደለ ከአመታት በኋላ ደግሞ የኢትዮጵያን ገበሬ ከመሬቱ አፈናቅሎ ለምለም መሬቱን በርካሽ ዋጋ ለባዕዳን ሽጧል፤ ከዚህ አልፎ ተርፎም የአባቶቻችን አጽም ያረፈበትን የአገራችን ዳር ድንበር ቆርሶ ለጎረቤት አገር ገጸ በረከት አቅርቧል። ይህ አገራቸዉንና የሚመሩትን ህዝብ በሚጠሉ ጠባቦች የተሞላ ድርጀት ባለፈዉ ሳምንት የኢትዮጵያን ህዝብ ብቻ ሳይሆን ደጋፊዎቹንና በአንቀልባ ታዝለዉ አስከዛሬ ያቆዩትን ምዕራባዉያን ጭምር ግራ ያጋባ ፀረ አገርና ፀረ ህዝብ እርምጃ ወስዷል። ድርጅት እያፈረሰና በፓርቲ ላይ የራሱን ተለጣፊ ፓርቲ እያቋቋመ ዛሬ ላይ የደረሰዉ ወያኔ ምርጫ የሚባል ድራማ በደረሰ ቁጥር የሚይዘዉ በሽታ ዘንድሮም ይዞት አንድነት ለፍትህና ለዲሞክራሲ ፓርቲንና መላዉ ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅትን አፍርሶ በምትካቸዉ የራሱን መኢአድና የራሱን አንድነት ለፍትህና ለዲሞክራሲ ፓርቲ ፈጥሯል። ይህ ወያኔ ከሰሞኑ የወሰደዉ የፖለቲካ እርምጃ በየትኛዉም አለም በተለይ የመድበለ ፓርቲ የፖለቲካ ስርዐትን እንከተላለን በሚሉ አገሮች ዉስጥ ታይቶም ተሰምቶም የማይታወቅ እጅግ በጣም ትልቅ የፖለቲካ ሸፍጥ ነዉ።
የወያኔን ታሪክ ተወልዶ ካደገበት ከደደቢት በረሃ እስከ ሚኒልክ ቤ/መንግስት ድረስ ያደረገዉን ጉዞ ስንመለከት ወለል ብሎ የሚታየን አንድ ሐቅ አለ፤ እሱም ወያኔ ሁሉንም ነገር በዘር መነጽር ብቻ የሚመለከትና ህዝብን በወዳጅና በጠላት ጎራ ለይቶ ወዳጅ አይደለም ያለዉን ሁሉ እንደ ሩሲያዊዉ ዮሴፍ ስታሊን እየገደለ የመጣ ድርጅት ነዉ። በእርግጥም ወያኔ ጫካ ዉስጥ እያለም ሆነ ዛሬ ከተማ ገብቶ የሚቃወመዉንና በሀሳብ የማይግባባዉን ድርጅትም ሆነ ግለሰብ እያፈረሰና እገደለ ባፈረሳቸዉ ድርጅቶች ምትክ ደግሞ የራሱን ተለጣፊ ድርጅት እየፈጠረ የመጣና ከዲሞክራሲያዊ አሠራርና ከስልጣኔ ጋር የማይተዋቅ ድርጅት ነዉ።
በመርፌ የተጠቃቀመ ቁምጣና ጥብቆ ለብሶ አስራ ሰባት አመት ጫካ ለጫካ የተጓዘዉ ወያኔ ጎንደር፤ ጎጃምና አምቦ እያለ ወደ አዲስ አበባ ሲጠጋ ከተገነዘባቸዉ ነገሮች አንዱ የለበሰዉ የተጠቃቀመ ቁምጣ የትም እንደማያደርሰዉና ለከተማ ኑሮ የሚስማማ አዲስ ልብስ እንደሚያሰፈልገዉ ማዉቁ ነዉ። በጥላቻ ተረግዞ በክፋት ላደገዉ ወያኔ ቢበቃዉም ባይበቃዉም ወይም ቢያምርበትም ባያምርበትም ይህንን ለከተማ ዉስጥ ኑሮ የሚያስፈልገዉን አዲስ ልብስ ለማዘጋጀት ብዙ ግዜ እልወሰደበትም። የሚሰርቅና የሚስቅ ምን ግዜም ተባባሪ አያጣም እንዲሉ ወያኔ የአዲስ አበባን መሬት የረገጠዉ ጦር ሜዳ ላይ የማረካቸዉን ወታደሮችና አገር ዉስጥ ያገኛቸዉን ደካማ ሰዎች ሰብስቦ በፈጠረዉ ኢህአዴግ በሚባል ፈረስ ጀርባ ላይ ተፈናጥጦ ነበር። ትግራይን ነጻ አወጣለሁ ብሎ ትግል የጀመረዉ ወያኔ ኢህአዴግን የፈጠረዉ ወያኔነቱን ለመተዉ ሳይሆን እራሱን በዚህ በኢትዮጵያ ስም በፈጠረዉ ድርጅት ዉስጥ ሸሽጎ እዉነተኛ ባህሪዩን ለመደበቅ ነበር።
ከግንቦት 1983 ዓም አስከ ግንቦት 1987 ዓም ድረስ የዘለቀዉንና በወያኔ የበላይነት ተጀምሮ ወያኔን በማንገስ የተጠናቀቀዉን የሽግግር መንግስት ወደ ኋላ መለስ ብሎ የቃኘ ማንም ሰዉ የወያኔን ሁለት ዋና ዋና መሠሪ ስራዎች በቀላሉ መመልከት ይችላል።
አንደኛ- ኦነግንና የደቡብ ህዝብ ንቅናቄን ጨምሮ አያሌ የፖለቲካ ፓርቲዎችንና ታዋቂ ግለሰቦችን አቅፎ ስራዉን የጀመረዉ የሽግግሩ መንግስት የስራ ዘመን የተገባደደዉ የኢትዮጵያን አንድነት ጥያቄ ያነሱ ግለሰቦችን በማሰርና ከወያኔ ቁጥጥር ዉጭ እራሳቸዉን ችለዉ ለመንቀሳቀስ የሞከሩ የፖለቲካ ድርጅቶችን ከሽግግሩ መንግስት በማባረር ነበር።
ሁለተኛ- ወያኔ የኋላ ኋላ እያደር ለመስራት ላቀዳቸዉ አገር የመበተንና ህዝብን የመለያየት ስራዎች እንዲያመቸዉ ከእያንዳንዱ የፖለቲካ ድርጅት ጀርባ የኢትዮጵያ ህዝብ ተለጣፊ እያለ የሚጠራቸዉን ድርጅቶች በራሱ አምሳል እየፈጠረ ማሰማራቱ ነዉ።
ባጠቃላይ ወያኔ የፈጠረዉ የሽግግር መንግስት ኢትዮጵያዊ አጀንዳና አገራዊ ራዕይ ይዘዉ የተንቀሳቀሱ ድርጅቶችንና ግለሰቦችን አጥፍቶ ወያኔን ዘለአለማዊ ንጉስ ለማደረግ ከመሞከሩ ዉጭ ሌላ ምንም ኢትዮጵያን የሚጠቅም ስራ አልሰራም።
ከሽግግሩ መንግስት በኋላ ወያኔ ተወዳዳሪዉም አሸናፊዉም እሱ ብቻ የሆነባቸዉን ሁለት ትርጉም የለሽ ምርጫዎችን አካሂዷል።እነዚህን ተወዳዳሪ የለለባቸዉን ሁለት ምርጫዎች በቀላሉ በማሸነፉ ህዝብ የወደደዉ መስሎት ልቡ ያበጠዉ ወያኔ ሦስተኛዉን አገራዊ ምርጫ ከመጀመሪያዎቹ ሁለት ምርጫዎች በተለየ መልኩ ለቀቅ አድርጎ ተቃዋሚ ፓርቲዎች በተወሰነ ደረጃም ቢሆን በነጻነት እንዲንቀሳቀሱ፤ መራጩን ህዝብ መቅረብ እንዲችሉና ወያኔን እራሱን ምርጫዉን አስመልክቶ ክርክር እንዲገጥሙት በሩን ከፈተላቸዉ። ነገሩ “የማይነጋ መስሏት” እንዲሉ ሆነና ሜዳዉም ፈረሱም ይሄዉና ብሎ የፊልሚያዉን ሜዳ የከፈተዉ ወያኔ የምርጫዉ ቀን ደርሶ በዝረራ መሸነፉን ሲሰማ በራሱ ሜዳና በራሱ ዳኞች ፍት ያሸነፉትን የህዝብ ተመራጮች ከየመኖሪያ ቤታቸዉ እያደነ አስሮ በአገር ክህደት ወንጀል ከሰሳቸዉ ። የሚገርመዉ ወያኔ በምርጫዉ ተወዳድረዉ በምስክር ፊት በአደባባይ ያሸነፉትን የህዝብ ተመራጮች በማሰር ብቻ አልተወሰነም። በወቅቱ የኢትዮጵያ ህዝብ እንደ አይኑ ብሌን ይመለከተዉ የነበረዉን ቅንጅት ለአንድነትና ለዲሞክራሲ ፓርቲን አፍርሶ እንደለመደዉ የራሱን ቅንጅት ፓርቲ ፈጥሮ ይበጃል ብሎ ላሰባቸዉ ደካማና ሆዳም ግለሰቦች አስረክቧል።
ይህ ቆየት ያለ በሽታዉ ዘንድሮም አገርሽቶበት አንድነትንና መኢአድን ለክፏቸዋል። ይህ ወያኔ ከሰሞኑ መኢአድና አንድነት ላይ የወሰደዉ እርምጃ እነዚህ ሁለት ፓርቲዎች በመጪዉ ምርጫ ላይ ያሸንፉኛል ከሚል ፍራቻ አይደለም። ወያኔ ምርጫዉ የሚካሄድበት ሂደት ብቻ ሳይሆን ህዝብ የሰጠዉ ድምጽ የሚቆጠርበትና የምርጫዉ ዉጤት ለህዝብ የሚገለጽበት መንገድ ሙሉ በሙሉ በቁጥጥሩ ስር እንደሆነና ይህንን ምርጫ ብቻ ሳይሆን የሚቀጥለዉንም ምርጫ ከሱ ዉጭ ሌላ ማንም እንደማያሸንፍ በሚገባ ያዉቃል። ወያኔ መኢአድንና አንድነትን የጥቃቱ ሰለባ ያደረጋቸዉ ህዝባዊ አላማቸዉንና አገራዊ ራዕያቸዉን በተለይ እነዚህ ሁለት ፓርቲዎች በኢትዮጵያ ህዝብ ታሪክ፤ አንድነትና እኩልነት ጥያቄ ላይ ያላቸዉን የጠራና የማያወላዉል አቋም እጅግ በጣም ስሚጠላ ነዉ። ከዚህ በተጨማሪ ወያኔ እንዲህ በአጭር ግዜ ዉስጥ መኢአድንና አንድነትን የጨፈለቃቸዉ እነዚህ ሁለት አንጋፋ ፓርቲዎች አዲስ አበባን ጨምሮ በየክልሉ የዘረጉት መዋቅርና ከህዘብ ጋር የፈጠሩት የቅርብ ግኑኝነት እንቅልፍ ስለነሳዉ ነዉ። ሌላዉ በፍጹም መርሳት የሌለብን ነገር ቢኖር ይዋል ይደር እንጂ ወያኔ እኛ ቀድመን ካላጠፋነዉ በቀር “ኢትዮጵያዊነት” ፤ “አንድነት” ወይም ፍትህና ነጻነት ብሎ የተነሳን ማንንም ኢትዮጵያዊ ግለሰብ ወይም ድርጅት ማጥፋቱ አይቀርም። በእርግጥም ከትናንት ወዲያ ቅንጀትን፤ ዛሬ ደግሞ መኢአድንና አንድነትን አፍርሶ የራሱን ተለጣፊ አሻንጉሊቶች የፈጠረዉ ወያኔ ነገ እነዚህ ፓርቲዎች የቆሙለትን አላማ የተሸከምነዉን ኢትዮጵያዉያን አንድና ሁለት እያለ ለቃቅሞ እንደሚያጠፋን ምንም ጥርጥር የለዉም።
ወያኔ አምስት አመት አየቆየ በሚመጣዉ የምርጫ ድርማ ከኢትዮጵያ ህዝብ ጀርባ ላይ እንደማይወርድ በ1997 ዓም ሰኔ ወርና በ 1998 ዓም ህዳር ወር በአዲስ አበባ አደባባዮች ላይ በወሰደዉ ፋሺስታዊ እርምጃ በግልጽ አሳይቶናል።ከላይ ከፍ ሲል ለመግለጽ አንደተሞከረዉ ወያኔ ፊታችን ላይ ባለዉ በ2007ቱ ምርጫ ወይም በተከታታይ በሚመጡት ምርጫዎች ተሸንፌ ከስልጣን እወርዳለሁ የሚል ምንም አይት ስጋት የለበትም፤ ምክንያቱም በምርጫዉ ጨዋታ ዉስጥ ተጫዋቹም ፤ ሜዳዉም ዳኛዉም ወያኔ ብቻ ነዉ። ዛሬ የወያኔን መሪዎች ያንቀጠቀጣቸዉና እንዳበደ ዉሻ ያገኙትን ሁሉ እንዲነክሱ ያደረጋቸዉ አገር ዉስጥና ከአገር ዉጭ የሚኖረዉ ኢትዮጵያዊ በተግባራዊ ስራዎች ላይ መናበብ በመጀመሩና በህዝባዊ እምቢተኝነቱና በህዝባዊ አመጹ ዘርፍ የሚደረገዉ እንቅስቃሴ ህዝባዊ ሙቀት አግኝቶ እየተጋጋለ በመምጣቱ ነዉ። ወያኔዎች እነሱንና የገነቡትን ዘረኛ ስርዐት ከኢትዮጵያ ምድር ጠራርጎ የሚያጠፋዉ የህዝባዊ አመጹና የህዝባዊ እምቢተኝነቱ ጎርፍ መሆኑን ካወቁ ቆይተዋል። ይህ ከሰሞኑ በማሰር፤ በመደብደብና ድርጅት በማፍረስ የወሰዷቸዉ እርምጃዎች የሚያሳዩን ወያኔዎች ህዝባዊ ጎርፉን ቢቻል ለማጥፋት አለዚያም ጉዳት በማያደርስ መልኩ ለመገደብ ያሚያደርጉትን ከንቱ ሙከራ ነዉ።
የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት፤ የኢትዮጵያ ወጣት፤ ገበሬና ሰራተኛ ባጠቃላይ የኢትዮጵያ ህዝብ ሆይ ትናንት ቅንጅትን አፍርሶ የራሱን መናኛ ቅንጅት የፈጠረዉ ወያኔ ዛሬም እንደገና አሉ የሚባሉትንና አገራዊ ራዕይ ይዘዉ የሚንቀሳቀሱትን አንድነትንና መኢአድን አፍርሶ በምትካቸዉ እንደጌኛ ፈረስ የሚጋልብባቸዉን የራሱን ሁለት መናኛ ፓርቲዎች ፈጥሮ መኢአድና አንድነት ብሎ ሰይሟቸዋል። ይህ በዋና ዋናዎቹ ዘረኛ የወያኔ ባለስልጣኖች ተጠንቶ በጥንቃቄ የተወሰደዉ እርምጃ ፓርቲዎቹ ህግ ስላላከበሩ ነዉ የሚል ሽፋን ይሰጠዉ እንጂ የምርጫ ቦርዱ ሊ/መንበር ሳያስቡት ከአፋቸዉ አፈትልኮ የወጣዉ እዉነት በግልጽ እንዳስቀመጠዉ ከምርጫዉ ጨዋታ ወጥተዉ እንዲፈርሱ በተደረጉት አንድነትና መኢአድ ፓርቲና ወያኔ በተለጣፊነት ባስጠጋቸዉ ሁለቱ ተለጣፊ ፓርቲዎች መካከል ያለዉ ልዩነት አንዱ ቆሜለታለሁ ለሚለዉ ህዝብ የሚታዘዝ ህዝባዊ ሌላዉ ደግሞ ሆዱን ለሚሞላለት ወያኔ የሚታዘዝ ሆዳም መሆናቸዉ ብቻ ነዉ።
የኢትዮጵያ ህዝብ ሆይ ወያኔ መብቴን ብለህ ስትጮህ በጥይት እየጨፈጨፈህ ነጻነት ስትለዉ በዱላ እየደበደበህና ሰላማዊ ሰልፍ ስትወጣ ደግሞ አፍሶ እያሰረህና ዉስጥ እግርህን ገልብጦ እየገረፈህ በሰላማዊ መንገድ የምታደርገዉን ትግል ምርጫ አሳጥቶሃል። ሆኖም ግልጽ በሆነ መንገድ እንነጋገር ከተባለ ወያኔ የትግል አማራጭ አያሳጣህም፤ ሊያሳጣህም አይችልም። ወያኔ እሱ እራሱ ህግ በሆነበት አገር ህጋዊ ወይም ሠላማዊ ትግል ብሎ ነገር ዋጋ ቢስ አንደሆነ ሁላችንም የተረዳን ይመስላል። ትግላችን ህዝባዊ እምቢተኝነት ነዉና ከዛሬ በኋላ ወያኔን ጥያቄ አንጠይቀዉም፤ አድርጉ የሚለንን አናደርግም፤ ሁኑ የሚለንንም አንሆንም። ትግላችን ህዝባዊ አመጽ ነዉና ከዛሬ በኋላ ወያኔ ሲገድለን እኛም እየገደልነዉ እንሞታለን እንጂ አንገታችንን ደፍተን የእሳት እራት አንሆንም። አዎ! ት ግላችን እምቢ ማለት ወይም ህዝባዊ እምቢተኝነት ነዉ፤ ትግላችን በወያኔ ላይ ማመጽ ወይም ህዝባዊ አመጽ ነዉ።