Thursday, 23 October 2014

የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት የሕዝብ ወገንተኝነቱን የሚያሳይበት ወቅት አሁን ነው!

 
ዘረኛውና ፋሽስታዊው የህወሓት አገዛዝ የኢትዮጵያን መከላከያ ሠራዊት በዘርና በፓለቲካ ወገንተኝነት በመከፋፈል ሹመቱና ጥቅማ ጥቅሙን ለራሱ ወገን፣ ችግሩንና መከራዉን ግን ለሌላው ኢትዮጵያዊ ያደለ መሆኑ ይታወቃል። በዚህም መሠረት ሳይማሩና ሳይሰለጥኑ የጄኔራልነት ማዕረጎችን በሙሉ ሰብስበው የወሰዱት የህወሓት አባላት መሆናቸው የአደባባይ ሚስጢር ነው።
በወያኔ መዳፍ ውስጥ እየተሰቃየች ባለችው ኢትዮጵያችን ውስጥ በዘርም ይሁን በፓለቲካ አመለካከት ከህወሓት የተለዩ ኢትዮጵያዊያን ቢማሩም ቢሰለጥኑም ለከፍተኛ አመራርነት እንደማይበቁ ባለፉት ሁለት አስርት ዓመታት ያየነው ነው። አገዛዙ ቅራኔ ውስጥ በገባባቸው ቦታ ሁሉ እየዘመቱ ሕይወታቸውን እየገበሩ ያሉት ግን በመካከለኛና ዝቅተኛ ማዕረጎች ያሉ ኢትዮጵያዊያን መኮንኖችና ብዙሃኑ የሠራዊቱ አባላት የሆኑ ወታደሮችናቸው። ብዙሃኑ የሠራዊት ክፍል አለቆቹን ከመጠበቅ ባለፈ ድምጹን ከፍ አድርጎ ለመናገር እንኳን የማይፈቀድለት ሎሌ ተደርጓል።
ለኢትዮጵያዊ ወታደር ለህወሓት ሎሌ ከመሆን በላይ የሞት ሞት የለም። ብዙሃኑ የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊቱ አባላት በጥቂት የወያኔ ሹማምንት የሚረገጥ መሆኑ የሠራዊቱን አባላት የግል ስብዕና ብቻ ሳይሆን በአጠቃላይ የሠራዊቱን ክብር ይነካል። የሠራዊታችን የህወሓት አገልጋይ መሆን የምንወዳት አገራችን ኢትዮጵያን ያዋርዳል። ይህ ዉርደት በዚህ ሁኔታ መቀጠል የለበትም።
ከእንግዲህ ጄኔራሎችና ሌሎችም የበላይ አዛዦች ሁሉ የአንድ አካባቢ ተወላጆች በሆኑበት ሠራዊት ውስጥ ተስማምቶ መኖር መቀጠል እያንዳንዱን የመከላከያ ሠራዊት አባል ሊያሰፍር ይገባል። የህወሓት ጄኔራሎች ጮማ በውስኪ ሲያወራርዱ፤ በህንፃዎች ግንባታ፣ በባንኮች ንግድ፣ በግብርናና በኢንዱስትሪ ዘርፍ ተሰማርተው ቢዝነሳቸውን ሲያጧጥፉ፣ ምስኪኖቹ የሠራዊቱ አባላት በኦጋዴን፣ በአፋር፣ በኦሮሚያ፣ በጋምቤላ፣ በአማራና በሌሎች የአገሪቱ ግዛቶች እየተወረወሩ ወገኖቻቸውን የሚፈጁበት ሥርዓት ማብቃት አለበት። የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት ብዙሃኑ አባላት ቤተሰቦቻቸው በችጋር እየተቆሉ የአዛዦቻቸው ሀብት ጠባቂ መሆናቸው ማክተም አለበት።
የኢትዮጵያ የመከላከያ ሠራዊት የጭለማ ዘመን ታሪክ እያበቃ መሆኑን የሚጠቁሙ ምልክቶች እየታዩ ነው። መሣሪያዎቻቸውን እንደያዙ የነፃነት ኃይሎችን የሚቀላቀሉ የሠራዊቱ አባላት ቁጥር ከጊዜ ወደጊዜ እየጨረመ መጥቷል። ሠራዊቱ ከሕዝብ ጎን እንደሚቆም ውስጥ ውስጡን የሚላኩ መልዕክቶች እየተበራከቱ መጥተዋል። ይህ አበረታች ዜና ነው፤ ግን በቂ አይደለም። ወያኔን ከውስጥም ከውጭም የምናጣድፍበት ጊዜው አሁን ነው። የነፃነት ኃይሎችን መቀላቀያ ጊዜ አሁን ነው፤ በሠራዊቱ ውስጥም በህቡዕ መደራጃ ጊዜ አሁን ነው። ይህን ጊዜ መጠቀም ብልህነት ነው።
ግንቦት 7: የፍትህ፣ የነፃነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ፣ ጥቂት የህወሓት ጥጋበኞች በብዙሃኑ የኢትዮጵያ የመከላከያ ሠራዊት ላይ የሚያደርሱት በደል ማብቃት አለበት ይላል። ግንቦት 7፡ የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት አባላት በሙስና የደለቡት፣ ትዕቢተኛና ጨካኝ መሪዎቻቸው ፍጹም ኢትዮጵያዊ ባህርይ የሌላቸው ፀረ ኢትዮጵያ ኃይሎች እንደሆኑ በመረዳት በተገኘው አጋጣሚ ሁሉ ክንዱን እንዲያነሳባቸው ጥሪ ያደርጋል። ከዚህ በተጨማሪ የኢትዮጵያ ሕዝብም የኢትዮጵያ የመከላከያ ሠራዊት አንድ ወጥ እንዳልሆነ እና በመካከለኛና ዝቅተኛ ደረጃ ያሉ መኮንኖችና አብዛኞዎቹ ወታደሮች የሕዝብ ወገን መሆናቸውን እንዲገነዘብ ያሳስባል። “አብረን ነው ዘረኛውና ፋሽስቱን ወያኔን ከኢትዮጵያ ጫንቃ ላይ አውርደን የምንጥለው” ስንል አብዛኛው የመከላከያ ሠራዊታችን ኢትዮጵያዊ ወገናችን እንደሆነ እና በወደፊቷ ኢትዮጵያ ግንባታ ውስጥም ጉልህ ሚና እንዲጫወት የምንፈልግ መሆኑን ግልጽ ማድረግ እንሻለን። የመከላከያ ሠራዊቱም የሕዝብ ወገንተኝነቱ በተግባር እንዲያሳይ ጥሪ እናደርጋለን። የኢትዮጵያ የመከላከያ ሠራዊት የሕዝብ አካል ነው፤ የሕዝብ ወገናዊነቱ በተግባር የሚያሳይበት ትክክለኛ ጊዜ ደግሞ አሁን ነው እንላለን።
ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ!!!

“እኔ ብቻ” ቢያክሙት የማይሽር የወያኔ በሽታ

 

ዘረኝነት፤ ጎጠኝነትና ዕብሪት የወያኔ አዲሰ ባህሪያት ሳይሆኑ አስራ ሰባት አመት ጫካ ዉስጥ በቆየባቸዉ አመታትና ዛሬም ከጫካ ወጥቶ አገር እየመራ በቆየባቸዉ ሃያ ሦስት አመታት አብረዉት የኖሩ መታወቂያ ካርዶቹ ናቸዉ። ዘረኝነት፤ አማራ ጥላቻና የትግራይ ሪፓብሊክ ህልም ዋና ዋናዎቹን የወያኔ መሪዎች ደደቢት በረሃ ከገቡ በኋላ በድንገት የለከፋቸዉ በሽታ ሳይሆን ከና ከልጅነታቸዉ ተጠናዉቷቸዉ አብሯቸዉ ያደገ በሽታ ነዉ። ወያኔ ጨካኝ ነዉ፤ ወያኔ ዉሸታም ነዉ፤ወያኔ ከሃዲ ነዉ፤ ወያኔ ለኢትዮጵያ ዳርድንበርና የግዛት አንድነት ደንታ የሌለዉ ባዕድ አካል ነዉ። እነዚህ ሁሉ የወያኔን ማንነትና ምንነት በትክክል የሚገልጹ የወያኔ በሽታዎች ናቸዉ። በዛሬዉ ቆይታችን በልዩ መነጽር አብረን የምንመለከተዉ የወያኔ በሽታ ግን በአይነቱ ከእነዚህ ከላይ ከተጠቀሱት በሽታዎቸ ጋር ተመሳሳይ ቢሆንም በጠባይና በአገላለጽ ግን ለየት ያለ ነዉ።
የኢትዮጵያ ህዝብ ለአመታት እንዳየዉም ሆነ ሀወሓትን መስረተዉ ለስልጣን ያበቁትና ህወሓት ለእነሱም አልበጅ ብሏቸዉ ጥለዉት የወጡት ግለሰቦች በቃልም በጽሁፍም እንደነገሩን ወያኔ የጫካ ዉስጥ ጠባዩን ዛሬም ያልለቀቀ መሆኑ ብቻ ሳይሆን ዛሬማ ጭራሽ ብሶበት ያየዉን ነገር ሁሉ ነጥቆ የራሱ ካላደረገዉ ወይም ሙሉ ለሙሉ ካልተቆጣጠረዉ አርፎ የማይተኛ ድርጅት ሆኗል። ብዙዎቻችን የወያኔ ስም በተነሳ ቁጥር ትዝ የሚለን ዘረኝነቱ ነዉ። በእርግጥም ወያኔ ግለሰብንና ግለሰቦችን ወይም የተለያዩ ቡድኖችን በዘር መነጽር ብቻ የሚመለከት ዘረኛ ድርጅት ነዉ። ሆኖም ወያኔንና ወያኔ የፈጠረዉን ዘረኛ ስርዐት ለመደምሰስ የሚደረገዉ ትግል የወያኔን ዘረኛ ገጽታ ብቻ ሳይሆን ሁሉንም የወያኔ ገጽታዎች ማጋለጥና መዋጋት አስፈላጊ ነዉ። ለምሳሌ ወያኔ በፕሮፓጋንዳዉ ይዋጋናል፤ በዲፕሎማሲ ዘርፍ ይዋጋናል፤ በማህበራዊ ሜዲያዉ ዘርፍ ለተሳዳቢዎች ገንዘብ እየከፈለ ይዋጋናል፤ ከዚህ በተጨማሪ በቁጥጥሩ ስር ባደረጋቸዉ ፍርድ ቤቶች፤ ፖሊስ፤ መከላከያና የደህንነት ተቋሞች አማካይነትም ይዋጋናል። አዎ ! ወያኔ በቁጥጥሩ ስር ባደረጋቸዉ ተቋሞች አማካይነት እንቅልፉን ትቶ ቀንና ማታ ይዋጋናል። ዉድ አድማጮቻችን እቺን ወያኔ በቁጥጥሩ ስር ባደረጋቸዉ ተቋሞች አማካይነት ይዋጋናል የምትለዋን አባባል ጠበቅ ያደረግነዉ አለምክንያት አይደለም። ዛሬ ብዙ የምናወራዉ ስለዚሁ “ሁሉን ነገር መቆጣጠር” ስለሚለዉ የወያኔ አባዜ ነዉ።
በወያኔ የበላይነት የተጻፈዉ የኢትዮጵያ ህገ መንግስት – የኢትዮጵያ ብሄር፤ ብሄረሰቦች፤ ህዝቦች የኢትዮጵያ ሉዓላዊ ሥልጣን ባለቤቶች ናቸዉ ይላል። ሆኖም የዚህ ሉዓላዊነት መገለጫ በሆነዉ ፓርላማ ዉስጥ 38 መቀመጫዎች ብቻ ያለዉ ህወሓት 509 መቀመጫዎች ያላቸዉን ከትግራይ ዉጭ ያሉትን ሌሎቹን የኢትዮጵያ ብሄረሰቦች የፖለቲካ ህይወት ሙሉ በሙሉ ይቆጣጠራል። የሚገርመዉ ወያኔ የሚቆጣጠረዉ የኢትዮጵያን ህዝብ የፖለቲካ ህይወት ብቻ አይደለም። የኢትዮጵያን የኤኮኖሚና የማህበራዊ ዘርፎችም ሙሉ በሙሉ በወያኔ ቁጥጥር ስር የወደቁ ናቸዉ። በአጠቃላይ ወያኔ ኢትዮጵያ ዉስጥ በዬትኛዉም ዘርፍ ከላይ እስከታች እሱ የማይቆጣጠረዉ ምንም ነገር እንዲኖር አይፈለግም። ዛሬ አገራችን ኢትዮጵያ ዉሰጥ በወያኔና በሁለቱ ግዙፍ የአገራችን ሐይማኖቶች መካከል ለአመታት የዘለቀዉ ንትርክ፤ አተካሮና ፍጥጫም የዚሁ የወያኔ ሁሉንም ነገር እኔ ብቻ ካልተቆጣጠርኩት የሚል ክፉ አባዜ ዉጤት ነዉ።
የወያኔ “እኔ ብቻ” አባዜ አዲስ አበባ ገብቶ ሥልጣን ከያዘ በኋላ የተጀመረ አዲስ እብደት ሳይሆን ወያኔ ገና በረሃ ዉስጥ እያለም ሰፊዉን የትግራይ ጫካ እኔ ብቻ ካልተቆጣጠርኩት የሚል በሽተኛ ድርጅት ነበር። ይህ ደግሞ ወያኔን ስለምንቃወመዉ ብቻ የምንለዉ ተራ ፕሮፓጋንዳ ሳይሆን ወያኔን ፈጥረዉ ለዛሬዉ ሥልጣን ካበቁትና ዛሬ የወያኔ አካሄድ አንገሽግሿቸዉ ይህንን ድርጀት በአይናችን አናይም ብለዉ ከማሉ የትግራይ ተወላጆች አንደበት የወጣ ሐቅ ነዉ። እነዚህ የወያኔን ታሪክ የተረኩልን ወይም በመጽሐፍ ጽፈዉ ያስነበቡን ግለሰቦች ወያኔ አንዳንድ እንደነሱ ጫካ ገብተዉ ትግል የጀመሩ የትግራይ ድርጅት መሪዎችን ለስብሰባ ጠርቶ ማታ በተኙበት ቦታ አንገታቸዉን እንዳረደ ሳይደብቁ ነግረዉናል። ወያኔ የትግራይን ጫካና በረሃ ብቻዬን ካልተቆጣጠርኩ በሚል ከኢዲህና ከኢህአፓ ጋር በተከታታይ ደም የተቃባ ድርጅት ነዉ። በተለይ ኢህአፓዎችን የትግራይ መሬት የናንተ አይደለምና ለቅቃችሁ ካልወጣችሁ እያለ ዛሬም ድረስ በየቦታዉ የሚጠቀምበትን “ክልሉን ለቅቃችሁ ዉጡ” የሚለዉን የዘረኝነት ፓሊሲዉን ገና ከጧቱ በረሃ ዉስጥ እያለ አሳይቶናል።
ወያኔ የትጥቅ ትግል ጀምሮ ጫካ ዉስጥ በቆየባቸዉ ግዜዎች ሁሉ ያሳየዉ ጠባይና አንዳንድ የወሰዳቸዉ እርምጃዎች ዛሬም ድረስ አብዛኛዉን የኢትዮጵያ ህዝብ ግራ ያጋቡና ዛሬም ድረስ መልስ ያልተኘላቸዉ እንቆቅልሾች ናቸዉ። ለምሳሌ ለህዝብ መብት፤ ነጻነትና እኩልነት እታገላለሁ ባዩ ወያኔ የሱን የመሰለ ተመሳሳይ አላማ የነበራቸዉን ኢትዮጵያዊ ድርጅቶች ህልዉናቸዉ እስኪጠፋ ድረስ በመሳሪያ ጭምር ተፋልሟቸዋል። በወቅቱ መሳሪያ አንግበዉ ለኤርትራ ህዝብ ነጻነት ይታገሉ የነበሩትን ጀብሃንና ከሻዕቢያን በተለይ ሻዕቢያን ግን ልክ እንደፈጣሪዉ ተመልክቶ ለፈጠሪ አምላክ ብቻ የሚሰጠዉን ስግደትና ማደግደግ ለሻዕቢያ ካለምንም ይሉኝታ ሰጥቷል። በትጥቅ ትግሉ ዘመን በነበረዉ የወያኔና የሻዕቢያ ግንኙነት የወያኔ መሪዎች ከሻዕቢያ ጋር ባልተስማሙባቸዉ ግዜዎቸም ቢሆን ወያኔ ሻዕቢያን እንደ ጌታዉ ማየቱንና ለሻዕቢያ መታዘዙን ያቆመበት አንድም ግዜ እንዳልነበረ ዛሬ በወቅቱ የህወሓት ማዕከላዊ ኮሚቴ አባላት የነበሩ ግለሰቦች በቁጭት የሚናገሩት ሐቅ ነዉ። የወያኔና የሻዕቢያ አላማ ተመሳሳይ እንዳልነበረ ለሁሉም ሰዉ ግልፅ ይመስለናል። ከሁለቱ የለየላቸዉ ከሀዲዎች ከመለስ ዜናዊና ከስብሀት ነጋ ዉጭ የአብዛኛዉ የህወሓት መሪና አባል አላማ የትግራይ ህዝብ መብትና ነጻነት በኢትዮጵያ የግዛት አንድነት ዉስጥ ተከብሮ እንዲኖር ነዉ። የጀብሀና የሻዕቢያ አላማ ግን ከዚህ ፍጹም የተለየ ነበር። ሆኖም ወያኔ ከሱ ጋር ተመሳሳይ አላማ ያላቸዉን ሌሎች ኢትዮጵያዉያን ድርጅቶች እየወጋ ለየት ያለ አላማ ላለዉ ሻዕቢያ ግን እጁን ሰጥቶ በወዶ ገባነት የኖረ ድርጅት ነዉ። ባጠቃላይ የአገራችን የክርስትና እምነት መሠረት በሆነችዉ ትግራይ ዉስጥ ተወልደዉ ያደጉት የወያኔ መሪዎች ሻዕቢያን እንዳምላካቸዉ ስለሚያዩ አጠጋባቸዉ ካለችዉ አክሱም ፅዮን ይልቅ ኤርትራ ድረስ እየሄዱ ለሻዕቢያ እንደ ታቦት ጎንበስ ብለዉ ሰግደዋል። ዛሬ እነዚህ የሻዕቢያ የእልፍኝ ዉስጥ ተላላኪዎችና ሻዕቢያ እንደ ልጅ ሳይሆን እንደ ማደጎ ልጅ ያሳደጋቸዉ ከሃዲዎቹ የወያኔ መሪዎች ናቸዉ ለኢትዮጵያ ህዝብ ነጸነት፤ እከኩልነትና ሰላም የሚታገሉ ድርጅቶችን ከሻዕቢያ ጋር ይሰራሉ እያሉ ክስ የሚያቀርቡት። ደንቆሮዎቹ የወያኔ መሪዎች ምንም ነገር ስለማይገባቸዉ ነዉ እንጂ የኢትዮጵያ ህዝብ እነሱ ሆን ብለዉ በቆፈሩት ጉድጓድ ዉስጥ ገብቶ ቁም ስቅሉን እያየ ነዉ። የዚህ ህዝብ ፍላጎት ከዚህ የምድር ላይ ገሀነም ከሆነ ጉድጓድ ዉስጥ መዉጣት ብቻ ነዉ። በሻዕቢያ በኩል ይዉጣ፤ በኬንያ ወይም በጂቡቲ በወያኔ እሳት የሚለበለበዉ የኢትዮጵያ ህዝብ እንደዚህ አይነቱን የቅንጦት ምርጫ ለማስተናገድ ግዜም ትዕግስትም የለዉም።
ወያኔ በ1983 ዓም አዲስ አበባን ተቆጣጥሮ የሽግግር መንግስት ሲያቋቁም ሙሉ በሙሉ እርግጠኛ ከሆነባቸዉ ነገሮች አንዱ የሽግግር መንግስቱን የማቋቋሚያ ሂደትም ሆነ በሚቋቋመዉ የሽግግር መንግስት ዉስጥ የሚወሰኑ ዉሳኔዎች ሁሉ በወያኔ ሙሉ ቁጥጥር ስር የሚወሰኑ ዉሳኔዎች መሆናቸዉን ማረጋገጥ ነበር። ለዚህ ነዉ የትግራይን ህዝብ ሰባትና ስምንት ግዜ እጥፍ የሚበልጠዉን የኦሮሞን ህዝብ እወክላለሁ የሚለዉ ኦነግ ገና ከጥዋቱ የሽግግር መንግስቱን ዘፈንና ጭፈራ ከተመለከተ በኋላ “ከዚህስ ጎመን በጤና” ብሎ ሁለተኛ ዙር የትጥቅ ትግሉን የጀመረዉ። በሽግግር መንግስቱ ዉስጥ ህገመንግቱን ማርቀቅን፤ የፌዴራል ስርዐት ማቋቋምንና የክልል አመሰራረትን ጨምሮ የሽግግር መንግስቱንና ከዚያም በኋላ የተፈጠረዉን የዉሸት መንግስት ሙሉ በሙሉ ተቆጣጥሮ ሁሉንም ስራ የሰራዉ ህወሐት ብቻ ነዉ፤ ሌሎቹ ከአጃቢነት ዉጭ ሌላ ምንም አይነት የጎላ ሚና አልነበራቸዉም።
በኢትዮጵያ የሙያ ማህበራት ታሪክ ዉስጥ ረጂም ታሪክና ጉልህ የአስተባባሪነትና የህዝባዊ ትግል መሪነት ሚና የነበራቸዉ ሁለቱ አንጋፋ የሙያ ማህበራት የኢትዮያ ሰራተኞች ማህበር (ኢሰማ) እና የኢትዮጵያ መምህራን ማህበር (ኢመማ) ነበሩ። እነዚህ ሁለት የሙያ ማህበራት ዛሬም መኖራቸዉ ጥርጥር ዉስጥ እስኪገባ ድረስ ደብዛቸዉ የጠፋዉ ወያኔ ሁለቱንም ማህበራት በቁጥጥሩ ስር በማድረጉ ነዉ። ኢትዮጵያ ዉስጥ በማቆጥቆጥ ላይ የነበሩ የሲቪክ ማህበራትና የዲሞክራሲ ግንባታ ተቋሞች ከዉጭ አገር ምንጮች እርዳታ እንዳያገኙ በማድረግ እነዚህ ተቋማት ወይ በወያኔ ቁጥጥር ስር እንዲደራጁ አለዚያም እንዲጠፉ አድርጓል። ዛሬ ኢትዮጵያ ዉስጥ ወያኔ እንቅስቃሴያቸዉን ብቻ ሳይሆን ህልዉናቸዉን ጭምር ሙሉ በሙሉ የማይቆጣጠር ምንም አይነት ህዝባዊ ተቋማት ወይም የሙያ ማህበራት የሉም።
ወያኔ ቄስ፤ ሼክ፤ መምህር፤ አሰልጣኝ፤ የአገር መሪ፤ ነጋዴ ወዘተ ሁሉንም ነገር መሆን የሚፈልግ ብቻ ሳይሆን መሆን የማይችለዉን ካልሆንኩ እያለ አገር የሚያበላሽ ችኮ ድርጅት ነዉ። ወያኔ በኢትዮጵያ ታሪክ ለመጀመሪያ ግዜ ከቤ/ክርስቲያን ህግና ደንብ ዉጭ የተሾመ ጳጳስ እያለ የራሱን ታጣቂ ጳጳስ የሾመ ዉግዝ ከመአሪዮስ የሆነ ድርጅት ነዉ። ወያኔ የክርስቲያን ተቋሞችን መቆጣጠሩ አልበቃ ብሎት ፊቱን ወደ መጂሊስ አዙሮ የእስላምና እምነት ተከታዮችንም ከእምነታቸዉ ዉጭ እምነት ካልሰጠኋችሁ ወይም ካልተቆጣጠርኳችሁ እያለ ያስቸገረ እኩይ ድርጅት ነዉ። ዛሬ ወያኔ ከእስልምና እምነት ተከታዮች ጋር የገባዉ ከፍተኛ ቅራኔና በጥቁር ህዝብ ታሪክ ዉስጥ በጥንታዊነቷ የምትታወቀዉ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤ/ክርስቲያን ህጋዊዉ ሲኖዶስና የወያኔ ሲኖዶስ ተብላ ለሁለት የተከፈለችዉ ወያኔ የሙስሊሞቹን መጅሊስና እቺን ጥንታዊት ቤ/ክርስቲያን ለመቆጣጠር እጅግ በጣም ፀያፍ የሆነ እርምጃ በመዉሰዱ ነዉ።
ኢትዮጵያ ዉስጥ የሐይማኖት ነጻነት ተረጋገጠ ብሎ የነገረን ወያኔ ባጳጳስ ላይ ጳጳስ ሾሞ የኢትዮጵያን ኦርቶዶክስ ቤ/ክርስቲያን የተቆጣጠረዉ ገና በጧቱ ነበር። ወያኔ ጳጳስ ብሎ የሾማቸዉ የአድዋዉ ተወላጅ አባ ጳዉሎስ ጳጳስ ሆነዉ ባገለገሉባቸዉ አመታት ሁሉ ወገባቸዉን ባጭር ታጥቀዉ ያገለገሉት የሰማዩን አባታቸዉን ሳይሆን የአድዋዉን ወንድማቸዉን መለስ ዜናዊን ነዉ። ፍርድ የማይሳነዉ እግዚአብሄርም ይህንን ምህረት የማይገባዉ በደል ተመልክቶ ነዉ እነዚህን ሁለት አመጸኞች መንፈቅ በማይሞላ ግዜ ዉስጥ ተራ በተራ የወሰዳቸዉ። ወያኔ አይናቸዉ ገንዘብና ንብረት ካየ በፍጹም አርፈዉ የማይተኙ ስግብግቦች ስብሰብ ቢሆንም የኢተዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤ/ክርስቲያንን ይቆጣጠራል ወይም ተቆጣጠረ ስንል ወያኔ የሚቆጣጠረዉ የቤ/ክርስቲያኒቱን ገንዘብና ንብረት አይደለም፤ ይልቁንም ወያኔ በቅርብ የሚቆጣጠረዉ የቤ/ክርስቲያኒቱን ዋና ዋና ዉሳኔዎችና ቤ/ክርስቲያንቱ በማህበረሰቡ ላይ ማድረስ የምትችለዉን ተፅዕኖ ነዉ። ዛሬ ወያኔ “ማህበረ ቅዱሳን” በሚል ስያሜ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤ/ክርስቲያን ስር የተደራጁ የእምነታቸዉ ቀናተኞችን ዉስጣችሁ ካልገባሁ እያለ የሚያዉካቸዉ አብሯቸዉ ፈጣሪን ለማምለክ ሳይሆን ያንን ሁሉንም ነገር ካልተቆጣጠርኩ የሚለዉን አባዜዉንና ስስቱን ለማርካት ሲል ብቻ ነዉ።
የሚገርመዉ ወያኔ የኢትዮጵያ ህዝብ ከሱ ቁጥጥር ዉጭ ሲተነፍስም ደስ ስለማይለዉ አንድ ለአምስት የሚባል የኮሚኒስቶች አደረጃጃት ይዞ መጥቶ ወጣቶችን፤ ሴቶችን፤ ሰራተኞችን፤ ገበሬዎችንና መምህራንን በአንድ ለአምስት አደራጅቶ አንዱ ስለሌላዉ በየቀኑ መረጃ እንዲሰበስብና ለበላይ አካላት እንዲያሳዉቅ አድርጓል። ስለሆንም ይህንን የወያኔን “እኔ ብቻ” የሚል አባዜ ከስሩ መንግሎ ለመጣል ብቸኛዉ መንገድ ወያኔን እራሱን በተባበረ ክንድ መንግሎ መጣል ነዉ እንጂ ዋልድባ፤ መጅሊስ፤ ወይም ማህበረ ቅዱሳን እያልን በተናጠል የምናደርገዉ ትግል ዋጋ የለዉም፤ ወይም ወያኔ ወደ እያንዳንዳችን አናት ላይ እስኪወጣ መጠበቅ የለብንም። ወያኔ ሌሎችን ሲያጠቃ “እኛ የለንበትም” ብለን ቁጭ ብለን እየተመለከትን የወያኔ ዱላ እኛጋ ሲደርስ የምናሰማዉ የድረሱልኝ ጩኸት ሰሚ አያገኝም – ማግኘትም የለበትም። የወያኔን ዘረኝነትና “እኔ ብቻ” የሚያሰኝ ክፉ በሽታ ለማጥፋት ብቸኛዉ መንገድ ወያኔንና ስርዐቱን በህዝባዊ ትግል ገርስሶ መጣል ብቻ ነዉ፤ ህዝባዊ ትግል ደግሞ መቀራረብን፤ መከባበርን፤ መተሳሰብን፤ አንድነትንና ትብብርን ይጠይቃል። እንግዲህ እንደ ትናንቱ ሁሉ የዛሬዉም ጥሪያችን ኑና ወያኔን በተባበረ ክንድ እንጣል የሚል ነዉ።

 
 
 
 
 
 
 

Tuesday, 7 October 2014

TPLF’s Minority Ethnic Monopoly of the Armed forces in Ethiopia ( A revisit after four years)

 


TPLF’s Minority  Ethnic Monopoly of the Armed forces in Ethiopia
( A revisit after four years)
 
The monopoly of key government decision making positions in Ethiopia by individuals of one ethnic group, the TPLF led Tigrean elite, over the past twenty three years has never had precedence in Ethiopian history.  This is even more an anomaly as the TPLF claims that it fought to champion ethnic equality in Ethiopia.

This monopoly of power is in staggering display particularly in the leadership of the armed forces of the country and the security agency.  What is even more becoming increasingly disquieting is that even the small number of non Tigreans that were thrown in to show some semblance of ethnic mix is fast fading.  Many Ethiopians today are not increasingly referring to the ruling political system in Ethiopia as an “ethnic apartheid” system without a good reason. When it comes to ethnic composition, the only lookalikes in history to the Ethiopian military today are only the armies of colonial forces and states and organizations under systems of apartheid.  With time, the TPLF has even stopped pretending that it is ruling over a multi ethnic country and continues to maintain an apartheid regime without even considering the serious consequences that this will bear on the country’s future.

There is widespread discontent among the regular army as well as rank and file officers that is predominantly drawn from the large non Tigrean ethnicity some of whom are referring to themselves as becoming slaves to a Tigrean dominated system. For several years now there is widespread and simmering discontent with this domination but questions related to these issues are not normally raised or discussed in public. Routine evaluation sessions the TPLF refers to as the “gimgemma”, conducted at all levels periodically and supervised by Tigreans, are used to stamp out these criticisms of this dominance and monopoly.  The TPLF would use one of its several labels – such words as hate politician, terrorist, ethnic chauvinist, narrow nationalist etc., on any one who questions the system or as they often call it, “exhibits a tendency” to oppose the status quo.  Many have perished for raising these questions even in good faith.   There have been several incidents of severe reprimands of individuals who raised these issues. Some members of the army who are now serving life in TPLF dungeons are those who raised such questions of the need to diversify the leadership.  Many did raise the question in good faith and sensing the discontent in the rank and file.  Some among the few high ranking non Tigrean officers have left the country and cited this slave like relations to even less qualified Tigreans superiors as their reasons for their leaving. Desertions by members of the regular army for this same reason are numerous and often remain unreported. Those who get the chance to tell their stories often speak of the indignity they underwent while in the army.

During the first few years of their rule, TPLF officials, including Meles Zenawi, tried to justify this monopoly of power by the dominance in terms of number and organization of the TPLF fighting force during the fighting to topple the Military dictatorship of Mengistu Hailemariam. The promise they often made was that the force will be ethnically diversified with time.  Now nearly a quarter of a century later, what we see is a more intensified and ethnically purified monopoly of power.  Merit and competence are forgone in favor of ethnicity so much that a good number of those in leadership positions have limited formal or technical education as compared to many of their subordinates.

Throughout the social and economic system, including the economy and key operations of government, we are witnessing an increasing dominance of the Tigrean elite.  The existence of a government within the government that is exclusively lead by ethnic Tigreans composed mostly of the leaders of the armed forces and the mafia like security gang is now an open secret among Ethiopians. Even the very few non Tigreans that are in leadership positions complain that they have only become conduits though which decisions made by the TPLF cabal are announced and implemented. These include people like Hailemariam Desalegn, who holds the nominal position of Prime Minister.

This staggering level of monopoly over national military power and intuitions is however displayed more blatantly in the composition of the leadership of the armed forces than probably elsewhere in the civilian administrative force. For Instance, Figure-1 shows that among the total of 64 highest military ranks in four departments and commands,  49 of them are Tigrians, two Agews and one from Mixed tribe, while the remaining number of Ormos, Amharas, and SNNPR are eight, four, and zero, respectively (for details see figure 1 and Annex-1-table 1).

Furthermore, the Military Affairs Team of Ginbot 7 has meticulously surveyed numerous divisions, regional commands, training academies and the defense headquarters in Addis Ababa and around the country; as a result it developed a detailed list of military leaders based on the most recent date gathered.  (See Annex-1:Table-1 &2).   According to this survey, the existing military governance system is highly skewed to one minority ethnic group, TPLF Tigrians. In general, the survey indicates that the system being followed by the current TPLF government is comparable to the old colonial and apartheid military organization systems, which now have become relics of history.





 

ሕወሓትና በትግርኛ ተናጋሪዎች ሙሉ ቁጥጥር ስር የወደቀዉ መከላከያ ሠራዊት ከአራት አመታት በኋላ በድጋሚ ሲፈተሽ

     
ሕወሓትና በትግርኛ ተናጋሪዎች ሙሉ ቁጥጥር ስር የወደቀዉ መከላከያ ሠራዊት
ከአራት አመታት በኋላ በድጋሚ ሲፈተሽ
ሕዝባዊ ሓርነት ወያኔ ትግራይ (ሕወሓት) ምን ያክል የኢትዮጵያን የፖለቲካ መዋቅሮች እንደሚቆጣጠር ለማወቅ በአገሪቱ የመከላከያ፣ የደህንነትና የፖሊስ ተቋሞች ዉስጥ ዋና ዋና የትዕዛዝ ሰጪና ቁጥጥር ቦታዎች ላይ በሀላፊነት የተቀመጡትን የትግራይ ተወላጆች ብዛት መመልከቱ በቂ ይመስለናል። የሕወሓት መሪዎች ስልጣን በያዙባቸዉ በመጀመሪያዎቹ ጥቂት አመታት ዉስጥ እየገነቡት ላይ ያለዉን ስርዐት መልካምና ሁሉን አቀፍ ስርዓት ለማስመሰል አንዳንድ ከነርሱ ቁጥጥር ዉጭ መተንፈስ እንኳን የማይችሉ የሌላ ብሄረሰብ ተወላጆችን አልፎ አልፎ ስልጣን ላይ አስቀምጠዋቸዉ ነበር። ዛሬ ሕወሓቶችን እራሳቸዉን እጅግ በጣም በሚያሳፍር መልኩ እነዚህ በጥንቃቄ ለቅመዉ ያመጧቸዉንም የሌላ ብሄረሰብ ተወላጆች ወደመጡበት መልሰዋቸዉ በሁሉም መስክ ቁልፍ የሆኑ የአገሪቱን  የስልጣን ቦታዎችን የሚቆጣጠረዉ የትግራይ ተወላጅ ሕወሓቶች ብቻ ሆነዋል። አያሌ ኢትዮጵያዉያን የህወሓትን አገዛዝ “ዘረኛ” አገዛዝ ነዉ ብለዉ የሚጠሩት ይህንን ሙልጭ ያለ በዘር ላይ የተመሰረተ ጭፍን አገዛዝ ተመልክተዉ ይመስለናል።
ዛሬ ኢትዮጵያ ዉስጥ ወያኔ ለፈጠረዉ ዘረኛ ስርዓት ብቸኛ ምሳሌ ሆኖ መቅረብ የሚችለዉ ደቡብ አፍሪካ ዉስጥ ነጮች የፈጠሩት ዘረኛ (Apartheid) ስርዓት ብቻ ነዉ። በኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት ዉስጥ በተለይ በቁጥሩ ከፍተኛ ብልጫ ያለዉና ትግርኛ ተናጋሪ ያልሆነዉ ሠራዊት እጅግ ያኮረፈ፤ የተቆጣና ያመረረ ሠራዊት ከመሆኑ የተነሳ እራሱን የሚመለከተዉ እንደ አገር መከላከያ ሠራዊት አባል ሳይሆን አንደ ህወሓት የቤት ዉስጥ አገልጋይ ባሪያ ነዉ። ይህ የሕወሓት ዘረኞች በሠራዊቱ ላይ የፈጠሩት የመገዛትና የበታችነት ስሜት በየቀኑ ከፍተኛ ቁጣና የዉስጥ ለዉስጥ ተቃዉሞ የሚገጥመዉ ቢሆንም ህወሓት በዘረጋዉ ከፍተኛ የአፈና መረብ የተነሳ የህዝብ መነጋገሪያ አርዕስት መሆን አልቻለም። የህወሓት መሪዎችም ቢሆኑ ይህንን ቁጣና ተቃዉሞ በሚገባ ስለሚያዉቁ “ግምገማ” እያሉ በሚያዘጋጇቸዉ መድረኮች ላይ እንደዚህ አይነቶቹን በእነሱ የበላይነት ላይ የሚነሱ ጥያቄዎችን ማስተናገድ ቀርቶ ጥያቄዎቹ እንዲነሱም አይፈቅዱም። አንዳንዴ ደፍረዉ እነዚህን ጥያቄዎች የሚያነሱ ግለሰቦች ሽብርተኛ፣ የደርግ ስርዐት ናፋቂዎች፣ ጠባብ ብሄረተኞች ወይም የጥላቻ ፖለቲካ አራማጆች የሚል ተቀጽላ ስም ይሰጣቸዋል። ዛሬ የዕድሜ ልክ እስራት ተፈርዶባቸዉ በተለያዩ የወያኔ እስር ቤቶች ዉስጥ የሚሰቃዩት ከፍተኛ ወታደራዊ መኮንኖች ለዚህ አሳዛኝ ሁኔታ የበቁት በመከላከያ ተቋሞች ዉስጥ ሠራዊቱን በየትኛዉም እርከን የሚመሩ መኮንኖች አመዳደብ ወታደራዊ አመራር ችሎታን፤ ልምድንና የብሄር ስብጥርን ያካተተ መሆን አለበት ብለዉ ደፍረዉ በመናገራቸዉ ነዉ።
ዛሬ የወያኔን መከላከያ ሠራዊት እየለቀቁ ከአገር የሚወጡ ከፍተኛ ወታደራዊ መኮንኖች ቁጥር በየቀኑ እየጨመረ በመሄድ ላይ ይገኛል። እነዚህ ወታደራዊ መሪዎች፤ የበታች መኮንኖች፤ ባለሌላ ማዕረጎችችና ተራ ወታደሮች ከጠላት እንከላከላን ብለዉ የማሉላትን እናት አገራቸዉን እየለቀቁ የሚወጡት በወያኔ ጦር ዉስጥ ስር የሰደደዉ ዘረኝነትና በዚህ ዘረኝነት ላይ የተመሰረተዉ አመራር የሚያደርስባቸዉ በደል አንገፍግፏቸዉ ነዉ። በየጎረቤቱ አገር ተሰድደዉ በችግር ላይ የሚገኙ ምርጥ የኢትዮጵያ የወታደራዊ ሳይንስ አዋቂዎች ሁሉም በአንድ ድምፅ የሚናገሩት ሠራዊቱ ዉስጥ ይደርስባቸዉ የነበረዉ ንቀትና ዉርደት የሰዉ ልጅ መሸከም ከሚችለዉ በላይ መሆኑን ነዉ።
ሕወሓትን ለረጂም ግዜ የመራዉ መለስ ዜናዊና ጓደኞቹ ሥልጣን በያዙባቸዉ በመጀመሪያዎቹ ሁለትና  ሦስት አመታት ጊዜያት ቁልፍ የሆኑ ቦታዎች  ሰዎች መያዛቸዉን አስመልክተዉ ሲናገሩ ህወሓት ለ17 አመታት የደርግን አምባገነናዊ ስርዓት ሲዋጋ የፈጠረዉ ወታደራዊና ድርጅታዊ ግዝፈት አብዛኛዉ የወታደራዊና የደህንነት አመራር ቦታ በህወሓት ታጋዮች አንዲያዝ ምክንያት ሆኗል ብለዉ ከተናገሩ በኋላ ይህ አሰራር በሂደት ሙሉ በሙሉ እንደሚቀይርና የኢትዮጵያ የፖለቲካና ወታደራዊ የሥልጣን ክፍፍል የአገሪቱን ብሄር ብሄረሰቦች ጥንቅር ያገናዘበ ይሆናል ብለዉ ተናግረዉ ነበር። ሆኖም ዛሬ ይህ ከተነገረ ከሃያ አመታት በኋላና ይህንን የተናገረዉ መለስ ዜናዊ ከዚህ አለም በሞት ከተለየ ከሁለት አመታት በኋላ የሕወሓት የሥልጣን ቁጥጥር ጭራሽ አጋሽቦ ዛሬ ኢትዮጵያ ዉስጥ ከትግርኛ ቋንቋ ዉጭ የሌላ ቋንቋ ተናጋሪዎች ወደ ሥልጣን አይመጡም የሚባልባት አገር ሆናለች። በኢትዮጵያ ዉስጥ ወያኔ በገነባዉ መከላከያ ሠራዊት ዉስጥ የዕዝ፤ የክፍለጦርና የመምሪያዎች አዛዥ ለመሆን ዋነኛዉ መለኪያ የትግራይ ብሄረሰብ ተወላጅና የሕወሓት ታማኝ አገልጋይ መሆን ነዉ እንጂ ችሎታ፤ ልምድ፤ ብቃትና የወታደራዊ ሳይንስ ክህሎት አይደለም። ችሎታ፤ ልምድና ብቃት መመዘኛ ሆነዉ የሚቀርቡት በመጀመሪያ ለሹመት የታጨዉ መኮንን የትግራይ ተወላጅ እና የሕወሓት ታማኝ አገልጋይ መሆኑ ከተረጋገጠ በኋላ ብቻ ነዉ።
የሕወሓት የስልጣን ሞኖፖሊ በወታደራዊ ደህንነት ተቋሞች ላይ ብቻ ተወስኖ አያበቃም። አብዛኛዉን የአገሪቱ የኤኮኖሚና ማህበራዊ ተቋሞችም ወይ ከላይ አለዚያም ከታች ሆነዉ የሚቆጣጠሩት የሕወሓት ታማኝ አገልጋይ ትግርኛ ተናጋሪዎች ናቸዉ። ዛሬ ኢትዮጵያ ዉስጥ ለይስሙላ የተቀመጠና ከተለያዩ ብሄር ብሄረሰቦች የመጡ ሰዎች የሚገኝበት አገዛዝ አለ፤ በዚህ አገዛዝ ዉስጥ ደግሞ አገሪቱን ወዳሰኘዉ አቅጣጫ በዘፈቀደ የሚዘዉረዉና ከትግርኛ ተናጋሪዎች ዉጭ ሌሎች የማይገኙበት በአገዛዙ ዉስጥ ሌላ ቡድናዊ አገዛዝ አለ። ዛሬ እነ ኃ/ማርያም ደሳለኝ፤ አባዱላ ገመዳና ደመቀ መኮንንን የመሳሰሉ ምስለኔዎች ስልጣን ላይ የተቀመጡ ነገር ግን የሕወሓት ጌቶቻቸዉ ከሚነግሯቸዉ ዉጭ በራሳቸዉ ምንም አይነት ትዕዛዝ መስጠት የማይችሉ አሻንጉሊቶች መሆናቸዉን እነሱ አራሳቸዉም የተገነዘቡት ይመስላል።
ግንቦት ሰባት- የፍትህ፤ የነጻነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ የዛሬ አራት አመት (እ.ኤአ.በ2009) በዘር የተደራጀዉን የወያኔ መከላከያ ተቋም አደረጃጀት ምን እንደሚመስል በመረጃ አስደግፎ ለአለም ህዝብ ማቅረቡ የሚታወስ ነዉ። ግንቦት ሰባት ይህ ይሻሻላል ወይም አደረጃጀቱ በሂደት ይለወጣል ተብሎ የተነገረለት የወያኔ መከላከያ ተቋም ጭራሽ ከድጡ ወደማጡ እያዘገመ መሆኑን በጥናታዊ መረጃዎች አስደግፎ እንደሚከተለዉ ያቀርባል። በዚህ ጥናት ዉስጥ የወያኔን መከላከያ ሠራዊት ይዘትና ቅርጽ በሚገባ የሚያዉቁ፤ ሠራዊቱን ለቅቀዉ የወጡና አሁንም በሠራዊቱ ዉስጥ በማገልገል ላይ የሚገኙ ከፍተኛ መኮንኖች ተሳትፈዋል። ከዚህ ቀጥሎ የሚቀርበዉ ሠንጠረዥ የተለያዩ የመከላከያ ተቋም የስልጣን ቦታዎችን፣ በስልጣን ቦታዎችን እነ ማን እንደተቀመጡና  የተወለዱበትን ብሄረሰብም ጭምር ያሳያል።
 
 

Monday, 6 October 2014

የሕወሓት/ኢህአዴግ መንግስት በ23 ዓመት ጉዞው ያፈራቸው ጄኔራል መኮንኖች ከወታደራዊ አመራር ሳይንስ ትምህርት እና ስልጠና አንፃር ሲመዘኑ/ በግንቦት 7 የወታደራዊ ጉዳዮች ቡድን የተዘጋጀ ጥናታዊ ፅሁፍ ክፍል 1

http://www.ginbot7.org/2014/10/06/%E1%8B%A8%E1%88%95%E1%8B%88%E1%88%93%E1%89%B5%E1%8A%A2%E1%88%85%E1%8A%A0%E1%8B%B4%E1%8C%8D-%E1%88%98%E1%8A%95%E1%8C%8D%E1%88%B5%E1%89%B5-%E1%89%A023-%E1%8B%93%E1%88%98%E1%89%B5-%E1%8C%89%E1%8B%9E/

አሜሪካ በኢትዮጵያ ላይ የያዘችውን ፓሊሲ ትመርምር


መስከረም 15 ቀን 2007 ዓም፣ የዩ. ኤስ. አሜሪካ ፕሬዚዳንት ባራክ ኦቦማና ባልደረቦቻቸው በአንድ በኩል ኃይለማርያም ደሣለኝና አለቆቹ በሌላ በኩል ሆነው የሁለትዮሽ ስብሰባ ተደርጎ ነበር። በዚህ ስብሰባ ላይ ፕሬዚዳንት ኦባማ ያደረጉት ንግግር የዲፕሎማሲ ጨዋነት ከሚጠይቀው ርቀት በላይ ተጉዘው ሸሪኮቻቸው ባልሠሯቸው ጀብዶች ማሞገሳቸው አሳዝኖናል። ፕሬዚዳንት ኦባማ ከላይ በተጠቀሰው ቀን ያደረጉት ንግግር ላይ በርካታ ስህተቶች፣ ህፀፆችና ግድፈቶች የያዘ ከመሆኑም በላይ አንዳንዱ አስተያየት የኢትዮጵያዊያንን ክብር የሚነካ ሆኖ አግኝተነዋል።
ፕሬዚዳንቱ ንግግራቸውን የጀመሩት “ኢትዮጵያ በዓለም ከሁሉም በላይ በከፍተኛ ፍጥነት በማደግ ላይ ያለች አገር ነች“ በሚል ዓረፍተ ነገር ነበር። የኢትዮጵያ ስታትስቲክስ ጽ/ቤት የፈጠራ ቀመሮች በዓለም ባንክ በኩል ዞረው በሚስ ሱዛን ራይስ ተቀነባብረው በባራክ ኦባማ አንደበት መስማት የሚያሳፍር ነው። የኢትዮጵያ ሕዝብ ኦባማ የተናገሩትን ዓረፍተ ነገር ከኢትዮጵያ ቴሌቪዥና ራድዮ ደጋግሞ ሰምቶ ሰልችቶታል። ኦባማ፣ ይህ የተሰለቸ ዓረፍተ ነገር በእሳቸው አንደበት ሲነገር ስለሚሰጠው ትርጉም ጥቂት ቢያስቡ ኖሮ ለእሳቸውም ለአሜሪካም የተሻለ ነበር ብለን እናምናለን። “በአንድ ወቅት ራሷን መመገብ ያቅታት የነበረችው አገር ዛሬ ከፍተኛ እድገት የሚታይባት ሆናለች፤ አሁን የግብርና ብቻ ሳይሆን [የኤሌክትሪክ] ኃይልንም በመሸጥ በቀጠናው ቀዳሚነት ይዛለች” ሲሉ ያሞካሿት ኢትዮጵያን ኢትዮጵያዊያን የማያውቋት መሆኑን፤ እሳቸው የሚያወድሷት ኢትዮጵያ በህወሓት ፕሮፖጋንዳ እንጂ በመሬት ላይ የሌለች መሆኑን ፕሬዚዳንት ባራክ ኦባማ ማወቅ ነበረባቸው። በአንፃሩ የእውነተኛዋ ኢትዮጵያ 70% ሕዝብ በድህነት ወለል በታች በሆነ ኑሮ ሕይወቱን እየገፋ እንደሆነ፤ የሚሊዮኖች ኢትዮጵያዊያን የእለት ጉርስ ምንጭ የአሜሪካና የአውሮፓ አገሮች እርዳታ መሆኑን ፕሬዚዳንት ኦባማ አያውቁም ማለት ይከብዳል። ፕሬዚዳንት ኦባማ የተናገሩለት የመብራት ኃይልም ለኢትዮጵያ ሕዝብ የተስፋ ተረት መሆኑን፤ ዛሬም የኢትዮጵያዊው የምሽት ኑሮ የሚገፋው በባትሪ፣ በሻማና በኩራዝ መሆኑን ፕሬዚዳንት ኦባማ አያውቁም ማለት ያስቸግራል።
ፕሬዚዳንት ኦባማ ከተናገሩት ውስጥ ትርጉም የሚሰጥ ነገር ቢኖር ስለ “ሰላም ማስከበር” የተናገሩት ነው። የህወሓት አገዛዝ፣ የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊትን ገንዘብ ባለበት እና አሜሪካ ወደ ፈለገችው ቦታ ሁሉ የሚልክ መሆኑ ይታወቃል። ስለሆነም የጦሩ የሰላም ማስከበር ሥራ ማሞካሸታቸው የሚጠበቅ ነው። እንዲያውም የፕሬዚዳንቱ ሙሉ ንግግር የተቃኘው ከዚህ አቅጣጫ ይመስላል። እንደዚያ ባይሆን ኖሮ የራሳቸው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ያወጣውን የሰብዓዊ መብት አያያዝ ሪፖርትን ውድቅ የሚያደርግ ነገር ባልተናገሩም ነበር። አንዳችም ነፃ ተቋማት በሌሉበት አገር ውስጥ ፍትሃዊ ምርጫ የሚባል ነገር ሊኖር እንደማይችል አውቀው ቀዳሚው ጥያቄዓቸው የሰብዓዊ መብቶች መከበር እና የነፃ ተቋማት ግንባታ ጉዳይ ባደረጉት ነበር። ፕሬዚዳንት ኦባማ ስለኢትዮጵያ ተጨንቀው ቢሆን ኖሮ የራሳቸው ስቴት ዲፓርትመን የዘንድሮውን የሰብዓዊ መብት አያያዝ ሪፓርት ያስታውሱ ነበር። ሪፓርቱን በማስታወሳቸው ብቻ በግፍ እየታሰሩ ስላሉት ዜጎች፣ በኦጋዴን፣ በኦሮሚያ፣ በጋምቤላ፣ በአፋር እና በአማራ እየተጨፈጨፉ ስላሉ ዜጎች፣ ስለ መሬትና የሀብት ዘረፋ፣ ስለፍትህ እጦት፣ ስለ ተቋማዊ ዘረኝነት እና ሌሎችም በርካታ ጉዳዮች እንዳነሱ ይቆጠር ነበር፤ ምክንያቱም ያ ሪፓርት የያዘው ይህንን ሁሉ ነው። ፕሬዚዳንት ኦባማ ግን የንግግራቸው ግብ ዘማች ወታደር ማግኘት በመሆኑ የራሳቸውን የስቴት ዲፓርትመንት ሪፓርት ትተው የወያኔን ሪፓርት ይዘው የቀረቡ አስመስሎባቸዋል። ይህ አካሄድ አሜሪካ ወደማትፈልገው የጦር አረንቋ የሚላኩ የሠራዊት አባላት ሊያስገኝ ቢችልም የሚያስከትላቸው ጉዳቶችም መታየት ነበረባቸው። የንግግራቸው ፈጣን አሉታዊ ውጤት ለማየት ቀናትም አልፈጀም፤ እነሆ በኦባማ አይዞህ ባይነት የተነቃቁት የህወሓት ገዳዮች ከኢትዮጵያ አልፈው በአሜሪካ ምድርም በኢትዮጵያዊያን ላይ መተኮስ ጀምረዋል።
የኦባማ ንግግር ትኩረት የፀጥታ ጉዳዮች ሆኖ ኢኮኖሚ የግኑኝነት ማሳለጫ ሆኖ ቀርቧል፤ የሰብዓዊ መብት አጠባበቅና የዲሞክራሲ ጉዳዮች ደግሞ ፈጽመው ተገፍተው ወጥተዋል። ይህ ንግግር አሜሪካ በኢትዮጵያ ላይ የምትከተለውን ፓሊሲ አመላካች ነው።
ግንቦት 7: የፍትህ፣ የነፃነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ በፀጥታ ጉዳይም ቢሆን አሜሪካ የያዘችው አቋም በረዥም ጊዜ የኢትዮጵያን ብቻ ሳይሆን የአሜሪካን ጥቅም የሚጎዳ ነው ብሎ ያምናል። ኢትዮጵያ ለአሜሪካ ከወታደር ምንጭነት በላይ የምታገለግል አገር ናት። ኢትዮጵያ ውስጥ ከራሱ ሕዝብ ጋር የታረቀ መንግሥት መኖር ለቀጠናው ሰላም እና ብልጽግና ወሳኝ ከመሆኑም በላይ የቀጠናው ሰላምና ብልጽግና የአሜሪካም ስትራቴጂያዊ ጥቅም ነው ብለን እናምናለን። የአጫጭር ጊዜ ጊዜዓዊ ጥቅሞችን ብቻ በመመልከት አምባገነኖችን መደገፍ አሜሪካን ምን ያህል ውድ ዋጋ እያስከፈላት እንደሆነ በዓይኖቻችን እያየነው ያለ ሀቅ ነው። አሜሪካ አምባገነኖችን መደገፏን ከቀጠለች ፈጥኖም ይሁን ዘግይቶ የምታገኘው እስካሁን ስታገኝ የነበረውን ውግዘትና የጽንፈኞች መጠናከር ነው። አሜሪካ የተሳሳተ ፓሊሲ በያዘችባቸው አገሮች ሁሉ ግንባር ቀደም ተጎጂዎች ለዘብተኞችና ዲሞክራቶች ሲሆኑ እየተጠናከሩ የሚመጡት ደግሞ ጽንፈኖች ናቸው። አሁንም አሜሪካ በኢትዮጵያ ላይ የያዘችውን ፓሊሲ የአገሪቱን የዲሞክራሲ ኃይሎችን የሚያዳክም እና ጽንፈኛ ኃይሎችን የሚያበረታታ እንደሆነ ከወዲሁ ሊጠን ይገባዋል።
ዩ. ኤስ አሜሪካ የምትመራባቸው የነፃነት፣ የእኩልነትና የፍትህ እሴቶች የግንቦት 7: የፍትህ፣ የነፃነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ እሴቶችም ናቸው። ኢትዮጵያዊያን እንደ አሜሪካ ዜጎች ሁሉ ፍትህን፣ ነፃነትን፣ እኩልነትንና ዲሞክራሲን ይሻሉ፤ እነዚህ መሻት ደግሞ መብታቸው ነው ብሎ ግንቦት 7 ያምናል፤ ለዚህም ይታገላል። አሜሪካ ይህን ትግል ማገዝ ይገባታል። በተግባር የምናየው ግን የዚህ ተቃራኒ ነው። አሜሪካ ለአጫጭር ጊዜ ጥቅም ስትል ከአምባገነን ኃይሎች ጋር ማበሯ የዓላማ ተጋሪዎቿን እያዳከመ መሆኑ የወቅቱ የዓለም ሁኔታ የሚመሰክረው ሀቅ ነው። በኢትዮጵያ ላይ እየተከተለችው ያለው ፓሊሲው ተመሳሳይ የረዥም ጊዜ መዘዝ እንዳያመጣ ያሰጋል። ይህ እንዳይሆን እርምት የሚገባው አሁን ነው።
ስለሆነም፣ ግንቦት 7፡ የፍትህ፣ የነፃነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ፣ ዩ. ኤስ. አሜሪካ በኢትዮጵያ ላይ የያዘችውን ፓሊስ እንደገና እንድትመረምር እና ዘረኛና አምባገነኑን የህወሓት አገዛዝን መርዳት እንድታቆም አበክሮ ያሳስባል።
ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ!!!

Saturday, 4 October 2014

ሰልጣኙንም አሰልጣኙንም ያንገሸገሻቸዉ ሥልጠና


አባትና የ10ኛ ክፍል ተማሪ ልጁ አምርረዉ ሲጨቃጨቁ እናት ትደርስና . . . . እባክሽ ልጄ አባትሽ የሚልሽን ለምን አትሰሚም ብላ ልጇን ትቆጣታለች። ልጅት ከተቀመጠችበት ትነሳና ምነዉ እማዬ ምኑን ነዉ የምሰማዉ፤ አባዬኮ እሱ እራሱ የማያዉቀዉን ነገር ላሳይሽ እያለኝ ነዉ ብላ ንግግሯን ሳትጨርስ በቁጣዉ ብዛት ፊቱ እንደ ፊኛ ያበጠዉ አበቷ ካንቺ ማወቅ ዬኔ አለማወቅ ይሻላል፤ ይልቅ የምልሽን ስሚ ብሎ ጮኸባት። ወጣቷ ተማሪ ወላጅ አበቷ ከስምንተኛ ክፍል በላይ ዘልቀዉ እንዳልተማሩ ብታዉቅም ለግዜዉ ማድረግ የምትችለዉ ምንም ነገር አልነበረምና እሽ አባዬ ብላ አባቷን መስማት ጀመረች። ይህ የአባትና የልጅ ስሚኝ አልሰማም ጭቅጭቅ ባለፉት ሁለት ወራት መሀይሞቹ የወያኔ ካድረዎችና የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች በየስልጠና አዳራሹ ያደረጉትን ፍጥጫ አስታወሰኝ። ይህ አብዛኛዉን ዕድሜያቸዉን ትምህርት በመማር በሳለፉት የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎችና በወጉ ስምንተኛ ክፍልን ባላጠናቀቁ የወያኔ ካድሬዎች መካከል በክረምቱ ወራት ተጀምሮ አሁን ድረስ የዘለቀዉ የ”አሰለጥናለሁ አታሰለጥንም” ትንግርታዊ ድራማ ወያኔ አስካሁን ከሰራቸዉ ድራማዎች በአይነቱ ለየት ያለ ድራማ ነዉ።
የወያኔ ምርጫዎች ምንም አይነት ዉድድር የማይታይባቸዉ ማንም ተወዳደረ ማንም ወያኔ ብቻ የሚያሸንፍባቸዉና ምርጫዎቹ ከመካሄዳቸዉ በፊት የት ቦታ እነማን ማሸነፍ እንዳለበቸዉ ተወስኖ ያለቀላቸዉ የለበጣ ምርጫዎች ናቸዉ። ወያኔ ግን “ሌባ ላመሉ ዳቦ ይልሳል” እንደሚባለዉ ምርጫዉ በቀረበ ቁጥር የሚያክለፈልፍ በሽታ ይይዘዋል። ኢትዮጵያ ዉስጥ በ1997ና በ2002 ዓም የተደረጉትን ምርጫዎችና እርግጠኞች ነን አሁንም በ2007 ዓም የሚደረገዉን ምርጫ የሚለያያቸዉ ነገር ቢኖር በእያንዳንዱ ምርጫ መኸል የአምስት አመት ልዩነት መኖሩ ነዉ እንጂ የምርጫዉን ዝግጅት፤ ሂደትና ዉጤት በተመለከተ ይህ ነዉ ተብሎ ሊነገር የሚችል ልዩነት የለም። ሁሉም ምርጫዎች የሚካሄዱት ወያኔ የምርጫ ተቋሞች፤ ሜድያዉንና ፍርድ ቤቶችን ሙሉ በሙሉ በሚቆጣጠርበት ሁኔታ ዉስጥ ነዉ። በዚህ ላይ ቅድመ ምርጫዎችን የሚቆጣጠረዉ፤ በምርጫዉ ብቸኛ ተወዳዳሪ የሆነዉና ህዝብ የሰጠዉን ድምጽ የሚቆጥረዉ ወያኔ እራሱ ነዉ። ይህም ሁሉ ሆኖ ወያኔ ከሱ ዉጭ ማንም ምርጫዉን እንደማያሸንፍ በልቡ እያወቀ አምስት አመት እየቆጠረ የሚመጣዉ ምርጫ በቀረበ ቁጥር ግርግር መፍጠር ይወዳል። በ1997 በተደረገዉ ምርጫ ማንም አያሸንፈኝም ብሎ ሜድያዉንና የፖለቲካ ምህዳሩን ትንሽም ቢሆን ለቀቅ አድርጎ የነበረዉ ወያኔ በ2002 ዓም ይጋፉኛል ብሎ የጠረጠራቸዉን ሁሉ ማሰር፤ መደብደብና እንቅስቃሴያቸዉን መግታት ጀመረ። አሁን በ2007 ዓም ደግሞ ገና በግንቦት ወር ለሚካሄደዉ ምርጫ የኢትዮጵያን ወጣት ካልተቆጣጠርኩ በሚል ትልቅ ዘመቻ ጀምሮ በከፍተኛ በሁለተኛ ደረጃና ዩኒቨርሲቲ ዉስጥ የሚገኙትን የአገሪቱ ወጣቶች በሥልጠና ሰበብ ወያኔያዊ የፖለቲካ ጠበል እያጠመቃቸዉ ነዉ።
ብዙ ኢትዮጵያዊያን ወያኔን ዘረኛ ነዉ፤ ጎጠኛ ነዉ፤ ነብሰ ገዳይ ነዉ ይሉታል። አዎ እነዚህ ሁሉ የወያኔን ማንነትና ምንነት በትክክል የሚያሳዩ ቃላት ናቸዉ። ወያኔ ግን ከእነዚህ ዉጭ ሌሎች ብዙ መገለጫዎች አሉት፤ ለምሳሌ ወያኔ መዋሻት የማይሰለቸዉ ዉሸታም ነዉ፤ ዕኩይ ነዉ፤ ጨካኝና የለየለት መብት ረጋጭም ነዉ። እነዚህ የወያኔ ባህሪያት ሁሉ ያናድዱናል ወይም ያስቆጡናል እንጂ አይገርሙንም ወይም እየኮረኮሩ አያስቁንም። ጉደኛዉ ወያኔ የሚገርሙና የሚያስቁ ባህሪያትም አሉት። ወያኔ የቁጥር ጨዋታ ይወዳል፤ በተለይ ከቁጥርና ከቁጥርም በዛ ካለ ቁጥር ጋር ለየት ያለ ፍቅር አለዉ። ለምሳሌ የኢትዮጵያ የአገር ዉስጥ ምርት ከዉጭም ከዉስጥም ተገፍቶ 5% ከጨመረ ወያኔ የሚነግረን 10% አደገ ብሎ ነዉ። ኢትዮጵያ ዉስጥ የትምህርት ጥራት ተንኮታኩቶ ከመዉደቁ የተነሳ ከዩኒቨርሲቲ ተመርቀዉ ወደ ስራ አለም በሚገቡ ተማሪዎችና የሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸዉን ጨርሰዉ ኮሌጅ በሚገቡ ተማሪዎች መካከል ያለዉ ልዩነት ትንሽ ነዉ፤ ወያኔ ግን በኔ ዘመነ መንግስት የዩኒቨርሲቲዉ ብዛት ብቻ ሳይሆን ከዩኒቨርሲቲ የሚመረቁ ተማሪዎች ብዛት ከ300% በላይ አደገ እያለ ይፏልላል። ካለፈዉ ሐምሌ ወር ጀምሮ ያለፍላጎታቸዉና ያለፈቃዳቸዉ በግድ ወደ ሥልጠና ማዕከላት እየገቡ የወያኔን ርካሽ ፕሮፓጋንዳ እንዲጋቱ የሚገደዱ ወጣቶችም ጉዳይ ይህንኑ ወያኔ ከቁጥርና ከብዛት ጋር የተጠናወተዉን ፍቅር የሚያሳይ ነዉ። ይህ ወያኔ በየክልሉ ሥልጠና ብሎ የጀመረዉ ቧልት የሰልጣኛቹን እዉቀት የሚያዳብር አይደለም ወይም ለአገራችን ለኢትዮጵያም በምንም መልኩ የሚጠቅም አይደለም። የሥልጠናዉ ብቸኛ አላማና ጥቅም በወጣቱ ላይ ተፅዕኖ በማሳደር የወያኔን አባላት ማብዛት ነዉ። ወያኔ ድርጅታዊ የፓርቲ ስራዎችን የሚሰራዉ መንግስታዊ ተቋሞችን በመጠቀም ከመንግስት ካዝና በሚወጣ ገንዘብ ነዉና እሱን የሚያስደስተዉ በሚሊዮን የሚቆጠሩ አባላት አሉት ተብሎ መነገሩ ነዉ እንጂ እነዚህ አባላት ታማኝ ይሁኑ አይሁኑ ወይም ድርጅታዊ ስራ ይስሩ አይስሩ ለወያኔ ጉዳዩ አይደለም።
ወያኔ በዕረፍት ላይ የሚገኙ የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎችን ከያሉበት በግድ አስመጥቶ ሥልጠና እንዲወስዱ ለማድረግ የወሰዳቸዉ እርምጃዎች ሁሉ በወያኔና በተማሪዎቹ መካከል ያለዉን ሰፊ የፖለቲካ ልዩነት አጉልቶ ከማዉጣቱ ባሻገር ይህ ሳይጀመር የከሸፈዉ ስልጠና ለወያኔ ምንም የፈየደዉ ፋይዳ የለም። እንዳዉም አብዛኛዉ ተማሪ የወያኔ መሪዎችን አንገት የሚያስደፋ ጥያቄዎችን በመጠየቅ ሥልጠና የሚያስፈልገዉ ለተማሪዎቹ ሳይሆን ለራሳቸዉ ለአሰልጣኝ ነን ባዮቹ መሆኑን በተግባር አሳይቷል። በብዙዎቹ የስልጠና አዳራሾች የወያኔ ካድሬዎች ተማሪዎቹ የሚጠይቁትን ጥያቄ መመለስ አለመቻላቸዉ ብቻ ሳይሆን ካድሬዎቹ በሚጠየቁት ጥያቄ እየተበሳጩ ጥርሳቸዉን ሲነክሱ ታይተዋል። በእርግጥም ጎንደር ዉስጥ የነበረዉን ጄኔሬተር ነቅላችሁ ዬት አደረሳችሁት ከሚል አፋጣጭ ጥያቄ ጀምሮ አንዳርጋቸዉ ጽጌን የሚመለከቱ ጥያቄዎችን በጠየቁ ተማሪዎች ላይ አሰልጣኝ ካድሬዎች “ከእናንተ ጋር በኋላ እንገናኛለን” እያሉ ሲዝቱ ተደምጠዋል።
ኢትዮጵያ ትናንትም ዛሬም ካለ ለጋሽ አገሮች ዕርዳታ መንፈቅ መዝለቅ የማትችል ደሃ አገር ናት፤ ሆኖም የወያኔ መሪዎችና ቤተሰቦቻቸዉ የሚዘርፉትን ገንዘብና አላግባብ የሚያባክኑትን የአገር ሃብት የተመለከተ ማንም ሰዉ ድርጊታቸዉ ከደሃዋ አገራችን ተጨባጭ ሁኔታ ጋር በፍጹም እንደማይገናኝ ለመገንዘብ ግዜ አይፈጅበትም። ወያኔ ገነባሁ ብሎ የሚያፈርሳቸዉንና በየስብሰባዉና በየጉባኤዉ ከሚያባክነዉ ግዙፍ የአገር ኃብት ዉጭ ከሰሞኑ ምንም አገራዊ ጥቅም በሌለዉና ሠልጣኞቹ አንፈልግም ብለዉ ለተዉት ሥልጠና የሚያባክነዉ የህዝብና የአገር ገንዘብ እጅግ በጣም ብዙ ነዉ። ለምሳሌ ለአሰልጣኝ ካድሬዎች ከሚወጣዉ የትርንፖርትና የዉሎ አበል ዉጭ ለእያንዳንዱ ሰልጣኝ ተማሪ በቀን የሚከፈለዉ ሃምሳ ብር ቁጥራቸዉ ከ600 ሺ በላይ በሆኑ ሰልጣኝ ተማሪዎች ልክ ሲሰላ እጅግ በጣም ብዙ ገንዘብ ነዉ።
ለመሆኑ ዜጎች የሚላስና የሚቀመስ አጥተዉ በሚራቡበት አገር፤ ወጣቶች ስራ ፍለጋ ያደጉበትን መንደር ጥለዉ ባሕር እየተሻገሩ በሚሰደዱበት አገርና የገንብዘብ እጥረት እየተባለ ብዙ ፕሮጀክቶች በሚታጠፉበት አገር ወያኔ ከየት እያመጣ ነዉ በመቶ ሚሊዮኖች የሚቆጠር ገንዘብ እየከፈለ ምንም እርባና የሌለዉ የፖለቲካ ሥልጠና ሥልጠናዉ በፍጹም ለማያስፈልገዉ የህብረተሰብ ክፍል የሚሰጠዉ? ደግሞስ ከዉጭ አገር ምንጮች ምንም አይነት የገንዝብ እርዳታ እንዳያገኙ በህግ የተከለከሉ የፖለቲካ ድርጅቶች የስራ ማስኬጃ ወጪያቸዉን መሸፈን አቅቷቸዉ በሚንገዳገዱበት አገር ምን ቢደረግ ነዉ ወያኔ የራሱን ፓርቲ ስራዎች በመንግስትና በህዝብ ገንዘብ የሚያሰራዉ?
የወያኔና የገንዝብ ጉዳይ ከተነሳ እነዚህ ጉደኞች ቢነገር ቢነገር የማያልቅ ከገንዘብ ጋር የተቆራኘ ብዙ የቆሸሸ ታረክ አላቸዉ። ከሰሞኑ ኢትዮጵያ ዉስጥ የአገሪቱን የአየር ሞገዶች ከዳር እስከ ዳር ያጨናነቀዉ ከዚሁ ከወያኔ የረጂም ግዜ ቆሻሻ ታሪክ ጋር የተያያዘዉ የገንዘብ ጉዳይ ነዉ። ከሰሞኑ የኢትዮጵያን ባንኮች፤ ትላልቅ መደብሮችና ዘመናዊ የመገበያያ አዳራሾች በብዙ መቶ ሚሊዮኖች በሚቆጠር ሀሰተኛ ገንዘብ ተጨናንቀዋል። ይህ ማን፤ መቼ፤ ከየትና እንዴት እንዳሰራጨዉ የማይታወቅ የሀሰተኛ ገንዝብ ዝርጭት ኢትዮጵያ ዉስጥ እያንዳንዱን ሰዉ እያነጋገረ ነዉ። የወያኔ ፖሊሶች ከየባንኩና ከየገበያ አዳራሹ በየቀኑ ከፍተኛ ቁጥር ያለዉ ሀሰተኛ የብር ኖቶች እየሰበሰቡ መሆናቸዉን ቢናገሩም ከዚህ ሀሰተና ገንዘብ ስርጭት በስተጀርባ የማን እጅ እንዳለበት ግን ምንም የተነፈሱት ነገር የለም። እንደዚህ ብዛት ያለዉ ሀሰተኛ የገንዘብ ኖት ደግሞ አቅምና እዉቀት በሌላቸዉ ተራ ወንጀለኞች የሚሞከር ወንጀል አይደለም። ለዚህም ይመስላል ብዙ ኢትዮጵያዉያን በዚህ ሀሰተኛ ገንዘብ ስርጭት ዉስጥ ያለምንም ጥርጥር የወያኔ ባለስልጣኖች እጅ አለበት ብለዉ በድፍረት አፋቸዉን ሞልተዉ የሚናገሩት። መቼም መሬት ቆፍሮ ቦምብ እየቀበረ በተቃዋሚዎች የሚያሳብበዉና በፈንጂ ህዝባዊ ተቋሞችን እያፈረሰ ሽብርተኛ ብሎ በፈረጃቸዉ ድርጅቶች ላይ ጣቱን የሚቀስረዉ ወያኔ የደረሰበትን ከፍተኛ የገንዘብ ጉድለት ለመሙላት ሀሰተኛ ገንዘብ አሰራጭቶ ሊያጠፋቸዉ በሚፈልጋቸዉ ሰዎችና ቡድኖች ላይ አያመካኝም ማለት አይቻልም። ለሁሉም የወያኔ ነገር አንቺዉ ታመጪዉ አንቺዉ ታሮጪዉ ነዉና ይህ የሀሰተኛ ገንዘብ ስርጭት የራሱ የወያኔ ስራ እንደሆነ ከራሱ ዉስጥ አዋቂ ምንጮች የምንሰማበት ግዜ ሩቅ አይደለም። በነገራችን ላይ ኢትዮጵያንና ኢትዮጵያዉያንን የሙጥኝ ብሎ ተጣብቆ የሚያሰቃያቸዉ የዋጋ ንረት መሠረታዊ መንስኤዉ መለስ ዜናዊ በህይወት ከነበረበት ግዜ ጀምሮ ከአገሪቱ የማምረት አቅም በላይ በሆነ መልኩ በገፍ እየታተመ ወደ ኤኮኖሚዉ ዉስጥ እንዲገባ የተደረገዉ የገንዘብ አቅርቦት ነዉ። ይህ ዘንድሮ ስሙን ቀይሮ “ሀሰተኛ የገንዝብ ስርጭት” ተብሎ አገራችንን የሚያምሳት በሽታም የዚሁ የተለመደ ወያኔ እያተመ የሚያሰራጨዉ የገንዘብ አቅርቦት ችግር አካል ለመሆኑ ምንም ጥርጥር የለዉም። አለዚያማ ወያኔ በነጋ በጠባ ሚሊዮንና ቢሊዮን እያለ የሚያባክነዉ ገንዘብ ከዬት ይመጣል?
ስልጠና በየትኛዉም ማህበረሰብ ዉስጥ የእዉቀትና የልምድ ልዉዉጥ ለማድረግ የሚረዳ ጠቃሚ ተግባር ነዉ፤ ሆኖም ስልጠና ሲባል አላማ፤ አትኩረትና ግብ ኖሮት በተወሰነ ቡድን ወይም ቡድኖች ላይ የሚያነጣጥር የእዉቀትና ልምድ መቀባበያ መሳሪያ ነዉ እንጂ እንዳዉ በጅምላ የአንድ አገር ህዝብ እንዳለ ተመሳሳይ ስልጠና ይዉስድ እየተባለ የሚደገስ የጨረባ ተዝካር አይደለም። ደግሞም ስልጠና አሰልጣኝና ሰልጣኝ ተግባብተዉና ሁለቱም ሚናቸዉን ወድደዉና ፈቅደዉ የሚካሄድ የጋራ እንቅስቃሴ ነዉ እንጂ ሠልጣኝ አልሰልጥንም ካለና አሰልጣኝ ደግሞ ጥያቄ የጠየቀዉን ሁሉ “ቆይ ጠብቀኝ” እያለ የሚዝትበት ከሆነ ነገሩ ሥልጠና መሆኑ ቀርቶ ጦርነት ይሆናል። ለመሆኑ ወያኔ የአገሪቱን ወጣቶች ሥልጠና ብሎ ሰብስቦ ምንድነዉ የሚላቸዉ? መልሱ ቀላል ነዉ። ከብዙዎቹ ሰልጣኞች አንደበት በግልጽ እንደሰማነዉ፤ የወያኔ ካድሬዎች በየስልጠናዉ አዳራሽ የሚናገሩት በሚቀጥለዉ ምርጫ ኢህአዴግን ካልመረጣችሁ የወደፊት ዕድላችሁ ይጨልማል፤ ከሐይማኖት አክራሪዎች እራሳችሁን አጽዱ ወይም ከሽብርተኛ ድርጅቶች ጋር እንዳትተባበሩ እያሉ ነዉ። ወያኔ በስልጣን ላይ በቆየባቸዉ አመታት ህይወቱ እንደ ሐምሌ ጨለማ የጨለመበት የኢትዮጵያ ወጣት ግን በየስልጠና አዳራሹ በተደጋጋሚ የሚጠይቀዉ እነሱ ሽብርተኛ ብለዉ ያሰሯቸዉን ጋዜጠኞችና የፖለቲካ ፓርቲ መሪዎች ባስቸኳይ እንዲፈቱና ወያኔዎችን እራሳቸዉን በሐይማኖት ጉዳይ ጣልቃ አትግቡ እያለ ነዉ።
ባለፈዉ የአዲስ አመት ዋዜማ ምሽት የግንቦት 7 የፍትህ፤ የነጻነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ ሊ/መንበር ለኢትዮጵያ ወጣቶች ኑና ለነጻነት፤ ለፍትህና ለእኩልነት አብረን እንታገል የሚል አገራዊ ጥሪ አድረገዋል። በየዘመኑ ለወገኖቹ መብትና ነጻነት መከበር ሽንጡን ገትሮ የታገለዉ የኢትዮጵያ ወጣት የነጻነት መሪዉ ያቀረበለትን የፍትህና የእኩልነት ትግል ጥሪ ረግጦ ከወያኔ ጋር በተላላኪነት ከሚያስተሳስረዉ ሥልጠና ጋር በፍጹም እንደማይተባበር ሁላችንም እርግጠኞች ነን። ዛሬ ዕድሜዉ ከ35 አመት በታች የሆነ ኢትዮጵያዊ ወጣት አብዛኛዉን ዕድሜዉን በወያኔ ስርዐት ዉስጥ የኖረ ወጣት ነዉ። ከዚህ በተጨማሪ የዚህ ዘመን የኢትዮጵያ ወጣት ወንድሙ፤ ዘመዱ ወይም የቅርብ ጓደኛዉ በወያኔ ነብሰ ገዳዮች ሲገደሉ በአይኑ እየተመለከተ ያደገ ወጣት ነዉ። ይህ ወጣት የወያኔ በደልና ግፍ የሚነገረዉ ወጣት ሳይሆን ይህንን በደልና ግፍ ለማቆም ቆርጦ የተነሳ ወጣት ነዉ። ይህ ወጣት ወያኔ ሥልጠና እያለ የሚፈጥርለትን አጋጣሚ ሁሉ እየተጠቀመ እራሱንና ወገኖቹን ነጻ ያወጣል እንጂ በሥልጠና ስም ከወያኔ በሚመጣለት ኮቶቶ እጅና እግሩን አስሮ የወያኔ ባሪያ ሆኖ አይኖርም። ለዚህ ቆራጥና አርቆ አስተዋይ ለሆነ ወጣት ያለን መልዕክት አይዞህ፤ በርታ፤ ጽና በድል የምንገናኝበትና የአገራችን ባለቤት የምንሆንበት ቀን ቅርብ ነዉ የሚል ወገናዊ መልዕክት ነዉ።