Thursday, 23 July 2015

“ኢትዮጵያና የአፍሪካ ቀንድ የወደፊት አቅጣጫዎች” አለክሳንድሪያ ቨርጂኒያ ኢሳት ባዘጋጀው ሲምፖዚየም ላይ ለውይይት የቀረበ


July 18, 2015
ብርሃኑ ነጋ (ዶ/ር)
ለግንቦት 9 (May 9th 2015) ስብሰባ ለውይይት የቀረበ
dr-berhanu-Negaመግቢያ:
የወያኔ ሥርዓት ለሀገሪቱ የማይበጅ፤ አገሪቱን አደገኛ ችግር ውስጥ የከተተና የበለጠ ጊዜ እስካገኘ ድረስ የሚያመጣው መዘዝ ዘላቂና መውጫ የሌለው ምስቅልቅል ውስጥ አገሪቱን የሚከታት መሆኑን ብዙው ህዝብ ይገነዘባል ማለት ይቻላል:: ስለ ሕዝቡ በጥቅል እንኳን መናገር ባይቻል የኢትዮጵያን ፖለቲካ በቅርብ የሚከታተሉና በተለይም በተቃዋሚ ድርጅቶች አካባቢ የሚገኙ ያገሪቱ ዜጎች በግልጽ የተረዱት ጉዳይ ነው:: በተለይ በቅርብ ጊዜ የወያኔ መንግሥት በተለያዩ የማህበረሰብ ክፍሎች ላይ የሚወሰደው የጭካኔ እርምጃ (ኦሮምያ፤ አማራ፤ አፋር፤ ሶማሊ፤ ጋምቤላ፤ ሲዳማ፤ሐረሪ፤…ወዘተ) እንዲሁም ሆን ብሎ ማህበረሰቡን በዘውግ ከፋፍሎ ለማባላት የሚያደርገውን መሰሪ እንቅስቃሴ በቅርብ የሚመለከቱ በዘውግ የተደራጁ የፖለቲካ ሀይሎች ሳይቀር የወያኔ አካሄድ ለነሱም የማይበጃቸው መሆኑን በመገንዘብ የስርዓቱ እድሜ ማጠር እንዳለበት ያምናሉ፤ ምንም እንኳን ይህንን ችግር በዘውግ መሰረት ላይ የቆመ ፖለቲካ የፈጠረው መዋቅራዊ ችግር አድርገው ሳይሆን የወያኔ የተለየ አምባገነናዊ ባህርይ የፈጠረው ችግር አድርገው የሚመለከቱት ቢሆንም:: በዚህ ጉዳይ ላይ በርዕዮተ ዓለም ላይ የተመሰረተ የፖለቲካ አደረጃጀትና እንቅስቃሴን በሚመርጡና የሀገሪቱን ፖለቲካ በዘውግ መነጽር በሚያዩ ኃይሎች መሀከል ያለው ሰፊና መትከላዊ ልዩነት እንደተጠበቀ ሆኖ የወያኔ ሥርዓት በቶሎ መቀየር እንዳለበት ሰፊ ሀገራዊ ስምምነት አለ ማለት ይቻላል::
ሌላው ሰፊ ስምምነት ያለ የሚመስለው ደግሞ በጥቅሉ የወያኔን ሥርዓት የሚተካው ምን አይነት ሥርዓት መሆን አለበት? የሚለው ላይ ነው:: ይህ ስምምነት “ጥቅል” ነው የሚባለው ሁሉም ምትኩ ሥርዓት “ዴሞክራሲያዊ” መሆን አለበት በሚለው ላይ ከመስማማቱ ባሻገር ይህ “ዴሞክራሲያዊ” ሥርዓት በኢትዮጵያ ሁኔታ ዘላቂና የተረጋጋ ማህበረሰብን ለመፍጠር ምን ተጨባጭ መልክ ይይዛል? በሚለው ዝርዝር ላይ ስምምነት አለመኖሩን ለማመላከትና ይህ ዝርዝር ጉዳይ ደግሞ በተግባራዊ ሂደት ላይ ወሳኝ ሚና ሊጫወት እንደሚችል ለማሳየት ነው:: ለምሳሌ ያክል ከላይ የተጠቀሰው: ፖለቲካው ዘውጌ መሰረት እንዲኖረው በሚፈልጉ ኃይሎችና ከዚያ ይልቅ በርዕዮተ ዓለም ላይ የተመሰረተ ፖለቲካ እንዲኖር በሚፈልጉት መሀከል ዴሞክራሲያዊ ስርዓት የሚይዘውን ተጨባጭ ቅርጽ በሚመለከት ያላቸው ልዩነት ትልቅ ትርጉም ያለውና በጥንቃቄ ካልተያዘ በጣም አወዛጋቢ ሊሆን የሚችል ልዩነት ነው:: ከስሜት የጸዳ፤እውነተኛ ዴሞክራሲያዊ ስርዓት ለዘላቂው መመስረትን ማዕከል ያደረገ ጠንካራ ውይይት የሚፈልግ ጉዳይ ነው:: ያም ሆኖ ግን የሚፈጠረው ሥርዓት ለተወሰነ ጊዜም ቢሆን እነኝህን ኃይሎች አቻችሎ ይዞ መሄድ ሊኖርበት እንደሚችል መገመትና ይህም አይነት ማቻቻል በተጨባጭ ምን መልክ ይይዛል የሚለውን በጥንቃቄ ማሰብ ብልህነት ብቻ ሳይሆን ተጨባጭ ፖለቲካ ውስጥ ከሚሳተፉ ኃይሎች የሚጠበቅ ነው:: ይህ ጉዳይ እራሱን የቻለ ውይይት የሚፈልግ ስለሆነ ወደፊት በሰፊውና ዝርዝር ተግባራዊ እንድምታው ላይ በማተኮር እንመለስበታለን:: ለዚህ ውይይት ያክል ግን ከሽግግሩ ጋር በተያያዘ አንድ አስፈላጊ ጉዳይ ላይ ብቻ እናተኩራለን:: የሽግግሩ ተዓማኒነት ጉዳይ ላይ::
የወያኔ ሥርዓት በቶሎ መወገድ አለበት፤ ይህንንም ሥርዓት መተካት ያለበት ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት መሆን አለበት በሚሉት ጉዳዮች ዙሪያ ሰፊ ስምምነት ካለ (በዝርዝሩ ላይ የሚኖሩት ልዩነቶች እንደተጠበቁ ሆነው)፤ ወዲያውኑ የሚነሳው ጥያቄ ደግሞ ታዲያ ይህን ሰፊ ስምምነት የሚያንጸባርቅ፤ ቢያንስ ይህን እምነት በኦፊሴል በሚያንጸባርቁ የፖለቲካ ኃይሎች ዘንድ ሰፊ ሀገራዊ የትግል መድረክ ለማዘጋጀትና በጋራ ለመታገል ለምን አስቸጋሪ ሆነ? በጋራ መታገል ባይቻል እንኳን እርስ በርስ መጠላለፉን ማስቆም ለምን አልተቻለም? የሚለው ጥያቄ ነው:: እዚህ ጉዳይ ላይ በሰፊው ሳንገባ ብዙ ጊዜ የሚቀርቡት ምክንያቶች የሚከተሉትን ይመስላሉ፤
በዘውጌ ፖለቲካ ዙሪያ በተደራጁና በሀገራዊ (ርእዮተ አለማዊ) አመለካከት ዙሪያ በተደረጁት መሀከል ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት በመፍጠር ዙሪያ ያሉ የተለያዩ አመለካከቶች የፈጠሯቸው ያለመተማመን (አንዱ ሌላውን በእውነት ለዴሞክራሲያዊ ሥርዓት መፈጠር የሚታገል መሆኑን መጠራጠር)፤
የሀገሪቱ የፖለቲካ ታሪክ ሁሌም በጉልበት ያሸነፈው አካል ፖለቲካውን በኃይል የሚቆጣጠርበት ታሪክ መሆኑና ይህም ያመጣው ያለመተማመንና የመሽቀዳደም ስሜት: (በምንም መልክ የፖለቲካ ሥልጣንን የያዘው ኃይል ከዚያ በኋላ ለሁሉም የተደላደለ የመወዳደሪያ ሜዳ ይፈጥራል ብሎ ባለማመን) ሥርዓቱ በዘላቂነት የሚመሰረትበትን መንገድ ከማሰብ ይልቅ መጀመሪያ ሥልጣን ላይ ማን ይወጣል በሚለው ላይ ያጠነጠነ መሆኑ::
የፖለቲካ ሥልጣን እያንዳንዱ ድርጅት በሕዝብ ዘንድ ባለው ተቀባይነት ወይንም ትግሉን ከዳር ለማድረስ በሚያደርገው አስተዋጽኦ መሰረት የሚደላደል (ስለዚህም በእውነተኛ ዴሞክራሲያዊ ምርጫ ወይንም የስራ አስተዋጽኦንና ክህሎትን ባማከለ ፍትሀዊ ክፍፍል) ሳይሆን ቢበዛ የፖለቲካ ኃይሎች የድርድር ውጤት ወይንም የጊዜው የኃይል አሰላለፍ ውጤት ነው ብሎ ከማመን የመጣ ሁሉም የራሱን ድርጅት አቁሞ ከሌሎች ጋር “በእኩልነት” ተደራድሮ እኩል የሚደለደል አድርጎ መገመት ያመጣው የድርጅቶች እንደአሸን መፍላት፤ይህ ደግሞ በበኩሉ የፈጠረው ማንኛውም የፖለቲካ ድርጅት ሌላውን አልፎ እንዳይወጣ በተቻለ መጠን የመከላከልና የማሰናከል አባዜ…ወዘተ
እነኝህንና ሌሎች መሰል ምክንያቶችን ደምረንና ቀንሰን ስናያቸው የሚያጠነጥኑት በሁለት አይነት አለመተማመኖች ላይ ነው:: የመጀመሪያው አለመተማመን ድርጅቶቹ (ከራስ ድርጅት በስተቀር) በእርግጥ ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ለመፍጠር ይፈልጋሉ ወይ? የሚለው መጠራጠር ሲሆን ሁለተኛውና የተያያዘው ደግሞ ባመለካከት ደረጃ ይህ ፍላጎት ቢኖራቸው እንኳን ባንድ አጋጣሚ የፖለቲካ ሥልጣንን ካገኙት በኋላ ለሁሉም እኩልና የተደላደለ ሜዳ የመፍጠር ፍላጎት ይኖራቸዋል ወይ? ያገኙትን ሥልጣን ውድድሩን አላግባብ ለማሸነፍ እንዲያስችላቸው ለራሳቸው በሚያደላ መልኩ ይጠቀሙበታል የሚለው ፍርሀት ነው:: እነኝህ ፍርሀቶች ምንም መሰረት የሌላቸው አይደሉም:: ከላይ እንደተጠቀሰው በታሪካችን የታየው ይህ ብቻ መሆኑ፤ በከፍተኛ ጥርጣሬ የተተበተበው ባህላችንና እያደር ያገዛዝ ስርዓቶች እያኮሰመኑት የሄዱት ማህበራዊ እሴታችን ሲታከልበት እንዲህ አይነት መጠራጠርና ፍርሃት ባይኖር ነበር የሚገርመው:: ስለዚህ ሂደቱ ያንን ፍርሃት በተጨባጭና አሳማኝ በሆነ መልኩ የሚቀርፍ መሆን ይገባዋል:: ከዚያም ባሻገር ግን ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት መፈጠሩን ዋና አላማቸው አድርገው የሚንቀሳቀሱና እነኝህ ፍርሀቶቻቸው ይህ ሥርዓት እንዳይፈጠር እንቅፋት ይሆናል ብለው ከልብ የሚያምኑ የዴሞክራሲ ወገንተኞች ያሉትን ያክል፤ እነሱ ሥልጣኑን እስካልያዙ ድረስ የሚኖረውን ምንም አይነት ውጤት (ሂደቱ ምንም ያክል አመርቂ ቢሆን) ኢዴሞክራሲያዊ ነው ብለው ከማጣጣል የማይመለሱ፤ ዴሞክራሲን ላፋቸው ያክል የሚናገሩት እንጂ ከልባቸው የማያምኑበት፤ የዴሞክራሲ ሳይሆን የስልጣን ወገንተኞችም በሰፊው የሚርመሰመሱበት የፖለቲካ ምህዳር ስለሆነ የዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታ ሂደቱ ጠንካራ መሰረት እስከሚይዝ ድረስ እነኝህን ጥርጣሬዎች የሚቀርፍ፤ የሀገራችንን የተወሳሰበ የፖለቲካ ትርምስ ከግምት ያስገባ የሽግግር ሂደት ማሰብ በጣም አስፈላጊ ነው:: ይህን ስናስብ ግን ሁሉም ሰው የሚስማማበት ሂደት ይኖራል ከሚል የዋህነት አይደለም:: ከላይ እንደተጠቀሰው የስልጣን ተካፋይ አልሆንንም ብለው እስካሰቡ ድረስ (ለምሳሌ በምርጫ ማሸነፍ ስለማይችሉ) ምንም አይነት ሂደትን የሚያጣጥሉ ይኖራሉ:: የዚህ ሂደት ተዓማኒነት በጣም የሚያስፈልገው እውነተኛ ዴሞክራሲያዊ ወገንተኞችን (ማለትም በነጻና ፍትሃዊ ምርጫ የህዝብ ውክልና ያገኘን የፖለቲካ ቡድን ማህበራዊ ተቀባይነት ወይንም ሌጂትመሲ ለመቀበል የማያቅማሙ) የሚያስማማ ሂደት እስከሆነ ድረስና ይህም በህዝቡ ዘንድ ተቀባይነት ያለው እስከሆነ ድረስ አመርቂ ሂደት ነው ብለን ልንወስደው እንችላለን::
ስለዚህ ሽግግሩን በተመለከተ እነኝህን ጥርጣሬዎች ሊቀርፍ የሚችልና ከሽግግሩ በኋላ በምርጫ የሚፈጠረውን ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ሙሉ ተዓማኒነት የሚያጎናጽፍ ሂደት ማሰብ ይገባናል:: ይህ ደግሞ ሶስት ደረጃዎች ያሉት ሂደት ነው:: የመጀመሪያው በሽግግሩ ወቅት የሚመሰረተውን “የሽግግር መንግሥት” ምንነት የሚወስነውና ይህ መንግሥት የህዝብ ውክልና ያለው መንግሥት እስከሚመሰረት ድረስ የሚሰራቸውን ስራዎች የሚመለከተው ነው:: ሁለተኛውና በጣም ወሳኙ ጉዳይ ደግሞ ከሽግግሩ ወቅት ወደ ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት የሚያሻግረውን የመጀመሪያውን ምርጫ ተዓማኒነት የሚመለከተው ነው:: ሶስተኛው ደግሞ ከሽግግሩ በኋላ የሚኖረው ሥርዓት ቅርጽን የሚመለከት ነው:: በነኝህ ጉዳዮች ላይ ግልጽ አመለካከትና አልፎም ሰፋ ያለ የፖለቲካ ሀይሎች ስምምነት መፍጠር ከተቻለ ወደ ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት የሚደረገውን ረጅም ጉዞና በዚህም መሰረት ዘላቂና የተረጋጋ ማህበረሰብ ለመፍጠር ያለንን እድል በእጅጉ ያሰፋልናል:: እነኝህ ሶስቱም የሽግግሩ አካሎች በጣም አስፈላጊ ቢሆኑም ለዚህ ውይይት የመጀመሪያውን ክፍል በሚመለከት ያሉትን ሥራዎች (የሽግግሩ ሥርዓት እንዴት ይቋቋማልና ምን ምን ሥራዎችን ያከናውናል የሚለውን) ለግንዛቤ ያክል ብቻ አስቀምጠን ለዚህ ውይይት በሁለተኛው ጉዳይ (የመጀመሪያውን ምርጫ በሚመለከት) እና በሶስተኛው ጉዳይ ማለትም የዴሞክራሲያዊ ሥርዓቱ ቅርጽ በእኔ እምነት ለምን ፕሬዜዳንታዊ መሆኑ እንደሚያስፈልግ ላይ በማተኮር አንዳንድ ለውይይት መተንኮሻ የሚሆን የመፍትሄ ሀሳብ እጠቁማለሁ:: ይህን የመፍትሄ ሀሳብ የማቀርበው በግሌ እንጂ በድርጅቱ የጸደቀ አመለካከት አይደለም:: ሀሳቡ ግን ሰፋ ያለ ማህበራዊ ተቀባይነት፤ በተለይም ደግሞ በዴሞክራሲያዊ ምሁራንና የፖለቲካ ሀይሎች ዘንድ ተቀባይነት ካገኘ ድርጅቱ ባለው አሰራር መሰረት ወደፊት የድርጅቱ ቋሚ ፖሊሲ አድርጎ ሊወስደው፤ ከዚያም ከሌሎች የፖለቲካ ድርጅቶችና ከመላው ማህበረሰቡ ጋር ሊወያይበትና የጋራ አቋም እንዲሆን ሊሰራበት ይችላል:: ለአሁኑ ግን እንደ አንድ “የህዝባዊ ምሁር” ሀሳብ ብቻ ተደርጎ ይወሰድ::
የሽግግር ሥርዓቱ አፈጣጠርና የሚሰራቸው ሥራዎች
የሽግግር ሥርዓት የሚባለው አሁን ያለው ሥርዓት ወድቆ የህዝብ ሙሉ ውክልና ያገኘ፤ በነጻና ፍትሃዊ ምርጫ የተመረጠ መንግሥት እስከሚመሰረት ድረስ ያለውን አጭር ጊዜ የሚመለከት ነው:: ይህ ጊዜ በመሰረቱ አዲሱን ሥርዓት ለመፍጠር ዝግጅት የሚደረግበት ጊዜ ነው:: የሽግግሩ ሥርዓት በራሱ ምንም የሕዝብ ውክልና የለውም:: አፈጣጠሩም በአብዛኛው ያለፈው ሥርዓት የወደቀበት ሂደት የሚወስነው ነው:: ለምሳሌ የወያኔ ሥርዓት የሚሄድበት አካሄድ እንደማያዋጣው አውቆና በጉልበት ተገፍቶ ከወደቀ የሚደርስበትን ኪሳራ በመፍራት ይህንን ክፍያ ለመቀነስ በሚል በሀገሪቱ ካሉ የፖለቲካ ሃይሎች ጋር በመደራደር የሚፈጠር የሽግግር ሂደት ከሆነ የሚይዘው ቅርጽና በሂደቱም የሚሳተፉ ሃይሎች አይነት፤ ወያኔ በጉልበት በሚፋለሙት ሀይሎች ተሸንፎ ወይንም በጠንካራ ህዝባዊ እምቢተኛነት ተገፍቶ ቢወድቅ ከሚፈጠረው የሽግግር ቅርጽና የሚሳተፉት ሃይሎች አይነት ይለያል:: ይህም ሆኖ ግን ሽግግሩ በርግጥም ወደ እውነተኛ ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት የሚደረግ ሽግግር ከሆነ በዚያ አጭር ጊዜ መሰራት ያለባቸው ቁምነገሮች በደንብ የታወቁ ናቸው:: በዚህም ምክንያት የሽግግሩ ሥርዓት ስኬት ባብዛኛው የሚለካው በሽግግሩ ውስጥ ምን አይነት ሃይሎች ናቸው የተሳተፉት በሚለው ሳይሆን (በምንም መልኩ ቢሰላ በዚህ የሽግግር ሂደት ውስጥ አልተሳተፍኩም ወይንም የሚገባኘን ሚና አልተጫወትኩም ብሎ የሚያምን የፖለቲካ ወይንም ማህበራዊ ሀይል መኖሩ የማይቀር በመሆኑ) እነኝህን ስራዎች በብቃትና የአዲስ ሥርዓት ምስረታ ዝግጅቱን ተአማኒና ሰፊ ማህበራዊ ተቀባይነት ባለው መልኩ በመስራቱ ላይ ነው:: ስለዚህ በዚህ ጽሁፍ ትኩረት የምናደርገው የሚሰሩት ስራዎች ላይ ነው:: ይህ ማለት ግን በሽግግሩ ሂደት ባሉት የሥልጣን እርከኖች የሚሳተፉት ሃይሎች ማንነትና አወቃቀሩ ምንም ትርጉም የለውም ለማለት አይደለም:: በተቻለ መጠን በሽግግሩ ወቅት የሥልጣን አወቃቀር ላይ ሰፊ የፖለቲካ ሃይሎችና ማህበራዊ ስብስቦች የሚሳተፉበት መሆኑ የሽግግሩን ወቅት ስራ የበለጠ ተዓማኒ የማድረግ እድል አለው:: ሽግግሩን የማቆም ታሪካዊ እድል ያገኙ ኃይሎች ይህን አጥብቀው ሊያስቡበት ይገባል:: ዋናው ትኩረት መሰጠት ያለበት ግን የሚሰሩትን ሥራዎችና የሚፈጠሩትን ተቋማት በርግጥም ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ለመፍጠር ሁኔታውን የሚያመቻቹ መሆኑን ማስረገጡ ላይ ነው::
1) በሽግግሩ ወቅት (ሙሉውን ጊዜ) በጊዜያዊው መንግሥት የሚሰሩ ሥራዎች
ከላይ በጥቅሉ እንደተጠቀሰው በሽግግሩ ጊዜ በዋናነት የሚሰራው አዲሱን ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ለማዋለድ የሚሰራው ስራ ነው:: ይህ ማለት በዚህ ወቅት ምንም አዘቦታዊ (routine) የመንግሥት ሥራዎች አይሰሩም ማለት አይደለም:: በጉዳዩ ላይ ብዙ ያሰቡበት ተመራማሪዎች እንደሚስማሙበት በዚህ ወቅት በማህበረሰቡ ላይ ዘላቂ ውጤት ያለው የመንግሥት ፖሊሲ ነክ ስራ ሳይሆን በተቻለ መጠን ውጤታቸው ከሽግግሩ ጊዜ የማያልፍ ስራዎች ይሰራሉ:: በዚህ ዝርዝር ላይ ክርክር ሊኖር ቢችልም ይህ እጅግ አወዛጋቢ ስላልሆነ ብዙ ትኩረት የሚያሻው ስራ አይደለም:: ይልቁንም ትኩረት የሚያሻው አዲሱን ሥርዓት በማዋለድ ሂደት ላይ ዘላቂ እንድምታ የሚኖራቸው ጉዳዮች ላይ ስለሆነ እነሱ ላይ እናተኩር:: እነኝህ ስራዎችም በራሳቸው እርስ በርስ የተገናኙ ግን ለመረዳት እንዲመች በሁለት ከፍለን ልናያቸው የሚገቡ ስራዎች አሉ:: እነኝህም የመጀመሪያው በሽግግሩ ወቅት መሰራት ያለባቸው ለቋሚው ሥርዓት መሰረት የሚሆኑ መሰረታዊ ስምምነቶችና ተቋማት ናቸው:: ሁለተኛው ደግሞ በሽግግሩ ወቅት ማህበረሰቡን ለቋሚው ሥርዓት የሚያዘጋጁና የማህበረሰቡን ስነልቦና የሚቀርጹ ተቋማትና ስነልቦናዊ ድባብ የመፍጠሩ ስራ ነው:: እነኝህ ሁሉም ስራዎች ግን ባንድ መልኩ ወይንም በሌላ ከላይ የጠቀስኳቸውን የጥርጣሬና ያለመተማመን መንፈስ የሚሰብሩ መሆን ይገባቸዋል::
ሀ) ለቋሚው ሥርዓት የማእዘን ድንጋይ የሚሆኑ መሰረታዊ ስምምነቶችና ተቋማት
እዚህ ላይ በመጀመሪያና በዋናነት የሚጠቀሰው የቋሚውን ሥርዓት የጫወታ ሕግ የሚያስቀምጠው የሕጎቹ ሁሉ የበላይ የሆነው ሕገ መንግሥት ነው:: ይህ ሰነድ ወሳኝ የሆነውን ያክል በተለይ አሁን በኢትዮጵያ ያሉ የፖለቲካ ሃይሎችን ሁሉ በሚያስማማ መልኩ መቅረጹ (ወይንም ያለውን ማሻሻሉ) በጣም አስቸጋሪ ነው የሚሆነው:: ከምክንያታዊነት ይልቅ ስሜት፤ የዛሬንና የነገን ከማሰብ ይልቅ ባለፈው ታሪክ ላይ በመንጠልጠል ደጋፊዎችን በሲቃ ስሜት (passion) ማሰባሰብን መሰረት ያደረጉ የፖለቲካ ልሂቃን በሚርመሰመሱበት የፖለቲካ ምህዳር፤ በረጅሙ አማትሮ የሚያይ፤ ሰፋ ያለ ማህበራዊ ስምምነት ያዘለ ሕገ መንግሥት ማዘጋጀት እጅግ ከባድና የረጅም ጊዜ ራዕይን መሬት ከረገጠ የሰጥቶ መቀበል ፖለቲካ ጋር አዋህደው መጓዝ የሚችሉ አዲስ ስርዓት አዋላጅ ዜጎችን የሚፈልግ አስቸጋሪ ስራ ነው:: ይህ ሕገ መንግሥት ምን መምሰል አለበት የሚለው ጉዳይ ላይ እዚህ ጽሁፍ ውስጥ በሰፊው አልገባበትም ግን በጥንቃቄ መሰራት ያለበት፤ በፍጹም ልንተወው የማንችለው የሽግግሩ ዋና የቤት ስራ መሆኑን ጠቅሶ ማለፍ ይበቃል:::: ከዚህ ጋር በተያያዘ በአንድ ወሳኝና የሚያስፈልገውን የመተማመን ስሜት በመፍጠር በኩል ጠቃሚ ነው በሚለው ጉዳይ ላይ ግን ያለኝን አመለካከት ባጭሩ እሄድበታለሁ:: ባጠቃላይ በአካሄድ ደረጃ ሊባል የሚችለው ግን ይህ ውይይት የሽግግሩ ጽንስ ከመጀመሩ በፊት ጀምሮ በሕገ መንግሥቱ ላይ ያለመስማማት ምንጭ ሊሆኑ ይችላሉ በሚባሉት ጉዳዮች ላይ ምሁራንና የፖለቲካ ልሂቃን ካሁኑ ውይይት ቢጀምሩበት ጠቃሚ መሆኑን ነው:: ሌላው በሂደት ደረጃ የሚነሳውና እጅግ አስፈላጊ የሆነው፤ ሕገ መንግሥቱን የማዘጋጀት ሂደት ከተጀመረበት ጊዜ ጀምሮ ማህበረሰቡን በሙሉ በስፋት ማሳተፍ የሚችልና ቀጣይነት ያለው ነጻ ውይይት በማህበረሰቡ ውስጥ በመገናኛ ብዙሀን አማካኝነትም ሆነ በስብሰባዎች መካሄድ እንዳለበት አጽንኦት መስጠቱ ተገቢ ነው:: የዚህን ሂደት ከባድነት ስንገልጽ ግን የሚኖሩት ልዩነቶች ጠንካራ ስሜቶች የሚንጸባረቁባቸው ቢሆኑም ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት መመስረትን ማዕከል እስካደረጉ ድረስ ከሚያለያዩት ጉዳዮች የሚያስማሙት የሚበልጡ መሆናቸውን ማወቅና ማመንም ተገቢ ነው::
ከተለያዩ የአህጉራችን ተመክሮዎች እንዳየነውና የወያኔ ዘመን ፖለቲካ ማንንም በማያሞኝ መልኩ ግልጽ ያደረገው አንድ ነገር ቢኖር ሕገ መንግሥት በጹሁፍ ደረጃ መኖሩና ተግባራዊ መሆኑ ፍጹም የማይገናኙ ክስተቶች መሆናቸውን ነው:: ከዚህ አንጻር ጥሩ ሕገ መንግሥት መጻፍ በጣም ቀላሉ ነገር ነው::[1] ከላይ ሕገ መንግሥትን በማርቀቅና የማሕበረሰቡን ስምምነት እንዲያገኝ ማድረግ አስቸጋሪ ነው ያልነው በእርግጥ በተግባር የመተርጎም ፍላጎቱ አለ ብለን እስካመንን ድረስ ብቻ ነው:: ይህንን ካመንን ከባዱ የሽግግር ዘመን ሥራ የሚዘጋጀውን ሕገ መንግሥት በእውነት ተግባራዊ ለማድረግ የሚያስፈልጉትን የመንግሥት ተቋማት የመፍጠርና እነኝህ ተቋማት በሕገመንግሥቱ የተሰጣቸውን ስራ ለመስራታቸው በቀናኢነት የሚጠብቁ ባለሟሎችንና ዜጎችን በመንግሥት ውስጥም ሆነ ከመንግሥት ውጭ በብዛት ማፍራት ነው:: ከዚህ አንጻር ሕገ መንግሥቱ የሚይዘው ቅርጽ ላይ ያሉ ልዩነቶች እንደተጠበቁ ሆነው ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት የግድ የሚላቸውና በትክክል እንዲሰራ በጣም አስፈላጊ የሆነው የሥልጣን ክፍፍል ላይ በማተኮር በነጻነት እንዲሰሩ በጠንካራ መሰረት ላይ መቆም ያለባቸውን ዋና ዋና ተቋማት መዘርዘር እንችላለን:: ከነኝህም ውስጥ ዋናዋናዎቹ:
ፍርድ ቤቶችና ከዚያ ጋር የተያያዙ የፍትህ ተቋማት (ፖሊስ፤ የአቃቤ ሕግ መስሪያ ቤት…ወዘተ)
የመከላከያና የደሕንነት አካላት ከፖለቲካ ወገንተኛነት ተላቀው ሙያዊ ስራቸውን ብቻ እንዲሰሩ ማድረግ
ከምርጫ ጋር የተያያዘ ስራ የሚሰሩ መስሪያቤቶችን ሁሉ በተግባር ገለልተኛ ማድረግ (ይህ ጉዳይ በተለይ ከሽግግሩ ጋር የተያያዘ ስለሆነ በመፍትሄ ሀሳቡ ላይ በድጋሚ እንመለስበታለን)
በመንግሥት ባጀት የሚተዳደሩ የመገናኛ ብዙሀን ከስራ አስፈጻሚ አካሉ ነጻ በሆነ አካል ስር እንዲተዳደሩ ማድረግ
በመንግሥት ባጀት የሚተዳደሩ የትምህርት ተቋማት፤ በተለይም ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የአካዳሚ ነጻነታቸው በተጠበቀ መልኩ እንዲሰሩ ከስራ አስፈጻሚ አካሉ ነጻ ሆነው በቻርተር እንዲተዳደሩ ማድረግ…ወዘተ.
እነኝህና መሰል ተቋማት አዲስ የሚፈጠሩ ሳይሆኑ አሁንም ያሉ ናቸው:: አሁን የሚሰራበትንም ሕገ መንግሥት በመርገጥ ሁሉም የገዢው ፓርቲ እንደፈለገ የሚጫወትባቸው ያገዛዝ መሳሪያ ሆኑ እንጂ:: መሰረታዊ አወቃቀራቸው በሚቀረጸው ሕገ መንግሥት የሚገለጽ ቢሆንም በሽግግሩ ወቅትም የሚሰሩ ናቸው:: ስለዚህ በሽግግሩ ጊዜ እውነተኛ ዴሞክራሲያዊ ሥርዓትን በሚመጥን መልኩ በተግባር እንዲሰሩ የማድረጉ ሀላፊነት የሽግግር መንግሥቱ ነው:: የሽግግር ሂደቱ ተዓማኒነት ከሚለካባቸው መስፈርቶች አንዱና ምናልባትም ዋናው በነኝህ ተቋማት ላይ በሚያደርገው ማሻሻል ስለሆነ የሽግግር መንግሥቱ ትልቅ ስራው አድርጎ የሚወስደው ነው::
በሕገ መንግሥቱ ውስጥ ሊነሱ የሚችሉ የተለያዩ ጉዳዮች ላይ ሳልገባ ግን ከሚፈጠረው ሥርዓት ቅርጽ ጋር በተያያዘ (ይዘቱ ዴሞክራሲያዊ መሆኑ ላይ ስምምነት እንዳለ ተቀብዬ) በተለይ ደግሞ እንዲፈጠር አስፈላጊ ነው ያልኩት በዴሞክራሲያዊ ሀይሎች መሀል የሚኖርን መተማመን ለማጠናከርና የሚፈጠረው ሥርዓት በሂደት ጠንካራ ሀገራዊ መሰረት አንዲኖረው ስለሚረዳ ብቻ የሚፈጠረው ስርዓት ቅርጽ አሁን ካለው ፓርላሜንታዊ ሥርዓት ይልቅ ፕሬዜዳንታዊ ለምን ቢሆን እንደሚመረጥ አንድ ሁለት ሀሳቦችን ላቅርብ::
ሀ_1) ፕሬዜዳንታዊ ስርዓት በኢትዮጵያ ሁኔታ ለምን ይመረጣል?
በዚህ ጉዳይ ላይ የማቀርበው አጭር አስተያየት ንድፈ ሀሳባዊ አይደለም:: ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት የተለያዩ ቅርጾች ቢይዝም ዴሞክራሲያዊነቱን የሚያረጋግጡት መሰረታዊ ምንነቶች ተግባራዊ እስከሆኑ ድረስ ቅርጹ በራሱ ዴሞክራሲያዊነቱን ጥያቄ ውስጥ አይከተውም:: ቅርጹን የሚወስነው ደግሞ እያንዳንዱ ሀገር ወደ ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ሽግግር በሚያደርግበት ጊዜ ያለበት የራሱ ታሪካዊ፤ ፖለቲካዊና ማህበራዊ ተጨባጭ ሁኔታ ነው:: የንድፈ ሀሳብ ጉዳይ አይደለም:: በኢትዮጵያም ወደ ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት በምናደርገው ሽግግር ወቅት የምንመርጠው የዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ቅርጽ አሁን ሀገራችን ያለችበትን ተጨባጭ ሁኔታ በጥንቃቄ በመገምገም የትኛው ቅርጽ ነው ልንፈጥር የምንፈልገውን ሥርዓት በተሻለ መደላደል ላይ ሊያስቀምጥልን የሚችለው የሚለውን ጥያቄ በመመለስ ነው:: ምንም እንኳን የዚህ የመጨረሻ ውሳኔ በሽግግሩ ወቅት የሚረቀቀውን ሕገ መንግሥት የሚያጸድቀው ህዝብ ቢሆንም፤ በዚያ ሂደት ውስጥ የሚሳተፉ ዴሞክራሲያዊ የፖለቲካ ሀይሎችና በእውቀታቸው የማህበረሰቡን ግንዛቤ መቅረጽ የሚችሉ ምሁራን ቢያንስ የሚቀርቡትን አማራጮች ጥቅምና ጉዳት በማሳየት በኩል ትልቅ ሚና ስለሚኖራቸው ይህንን ውይይት ካሁኑ መጀመሩ ጥቅም አለው ብዬ ስለማምን ነው እዚህ ጽሁፍ ላይ ባጭሩ የማቀርበው::
ያለፉት 24 አመታት የወያኔ “የውሸት ፓርላሜንታሪ ስርዓት” ዴሞክራሲያዊ ሥርዓትን ለመመስረት ከምር የሚፈልጉ ሀይሎችን ሊያስተምሩ የሚገባቸው ሁለት ወሳኝ ተመክሮዎች ያሉ ይመስለኛል:: አንደኛው ሁሉም የሚያውቀው በተግባርና በንድፈ ሀሳብ መሀከል ያለው ከውቅያኖስ የሰፋ ልዩነት ነው:: ስለዴሞክራሲ መለፈፍና በተግባር ዴሞክራሲያዊ መሆን ለየቅል መሆናቸውን ያለምንም ጥርጥር በአይናችንና በኑሯችን አይተነዋል:: ሁለተኛው ትምህርት ደግሞ በንድፈ ሀሳብና በኦፊሴላዊ መዋቅር የተቀመጠን አካሄድ በተግባር ለመገርሰስ ምን ያክል ቀላል እንደሚሆንና የቅለቱ መጠን ደግሞ በስርዓቱ ቅርጽ ላይ ያሉትን ቀዳዳዎች በግልጽ ላልወጣውና ለተደበቀው እውነተኛ የፖለቲካ ሃይሎች ፍላጎት ማስፈጸሚያ ማዋል እንደሚቻል ነው:: በዚህ ሂደትም የአንድን ሥርዓት እውነተኛ ምንነት ሳይሆን ከላይ የለበሰውን የማስመሰያ ልብስ ብቻ ለማየት ለሚፈልጉ አገራዊም ሆነ ውጫዊ ሀይሎች ማማለያነት እንዴት ሊውል እንደሚችል በበቂ አይተናል:: የዚህ ክፍል ውይይት በኢትዮጵያ ሁኔታ በስልጣን ላይ የሚወጡ ኃይሎች የሚፈጠረውን መዋቅር ለጠባብ ጥቅማቸው እንዳያውሉት በትንሹም ቢሆን ለመከላከል የሥርዓቱን ቅርጽ ብዙ ቀዳዳ የሌለው እንዲሆን ለመሞከር ነው::
በተግባር በኢትዮጵያ እንደምናየው እውነተኛ ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ለመፍጠር የማይፈልጉ ኃይሎች የፓርላሜንታዊ ሥርዓትን ለማዋከብ (abuse) ከሚያስችላቸው ቀዳዳ አንዱ በቂ የሆነና የተለያዩ የሥልጣን አካሎችን መዋቅራዊ በሆነ መልክ መለያየት የሚችል የሥልጣን ክፍፍል ያለመኖሩ ነው:: በዚህ ሁኔታ የፓርላማው አባሎች ሥልጣናቸውንም ሆነ ተግባራቸውን የሚያዩትና የሚለኩት ለሥልጣን ካበቃቸው ፓርቲ ጥቅም አንጻር ብቻ ስለሚሆንና ጠንካራ የሆነ ተቋማዊ ተአማኒነት (institutional loyalty) ስለማይኖራቸው ፓርቲው ለመረጠው (በቀጥታ በህዝብ ያልተመረጠ) ስራ አስፈጻሚ አካል ተገዢ የሚሆኑበትን ሁኔታ ይፈጥራል:: ይህ ደግሞ ለዴሞክራሲያዊ ሥርዓት እጅግ አስፈላጊ የሆነውን ከስልጣን ክፍፍል ጋር የሚመጣውን የጎንዮሽ ተጠሪነት (horizontal accountability) ያዳክመዋል:: በፕሬዜዳንታዊው ቅርጽ ግን የስራ አስፈጻሚው አካል በመላው ህዝብ (ስለዚህም የመላውን ህዝብ ጥቅም ወደ ማስጠበቅ)፤ የህግ አውጭው አካል ደግሞ በያካባቢው ህዝብ ምርጫ ለየብቻቸው የሚሰየሙ መሆናቸውና (ስለዚህም ተጠሪነታቸው ለመረጣቸው አካባቢ ህዝብ) በዚህም ምክንያት የሚኖረው የተጠሪነት ልዩነት ተዓማኒነቱን ይበልጥ ወደ ተቋማዊ ተዓማኒነት እንዲያደላ ያደርገዋል የሚል እምነት አለኝ:: በዚህ ሁኔታ የሥራ አስፈጻሚውን ምርጫ ያሸነፈውና የሕግ አውጭውን ምርጫ ያሸነፈው አካል የተለያዩ ሊሆኑ የሚችሉባቸው ሁኔታዎች ይኖራሉ:: ይህ ሁኔታ በስራ አስፈጻሚውና በህግ አውጭው መሀከል ብዙ ንትርክ ሊያመጣና አስተዳደሩንም ሊያዳክመው ይችላል:: ይህ ግን በራሱ መጥፎ ነገር አይደለም:: ይበልጡንም በጀማሪ የዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ውስጥ የሰጥቶ መቀበል ፖለቲካ እንዲዳብር ይረዳል የሚል እምነት አለኝ::
ሁለተኛውና በተለይ በሀገራችን ሁኔታ ይህንን ቅርጽ እጅግ አስፈላጊ የሚያደርገው ባለንበት የታሪክ ሁኔታ የተፈጠረውን በዘውጌ ማንነትና በሀገራዊ ማንነት መሀከል ያለውን በቅጡ ያልተፈታ ግጭት በሂደት አገራዊ ማንነት እያደር እየተጠናከረ እንዲሄድ ያደርገዋል የሚል እምነት አለኝ:: የሀገራዊ ማንነት መጠናከር ደግሞ ለማንኛውም የሚሰራ ዴሞክራሲያዊ የፖለቲካ ማህበረሰብ በጣም አስፈላጊ ነው:: በፓርላሜንታዊ ሥርዓት መራጮች የሚመርጡት ያካባቢያቸውን ወኪል ብቻ ነው:: ያ ወኪል ላጠቃላይ ማህበረሰቡ የሚጠቅም መሪ ነው አይደለም በሚለው ላይ መራጩ ድምጽ የለውም:: በዋናነት ተዓማኒነቱ ለመረጠው አካባቢ ማህበረሰብ ነው:: በፓርላማው የተመረጡ ሰዎች (ብዙሀኑን መቀመጫ ያገኘው ፓርቲ ወኪሎች) በሚያደርጉት የስልጣን ድርድር ወይንም ፓርቲው በሚወስነው ውሳኔ ብቻ ነው የስራ አስፈጻሚውን ስልጣን የምትረከበው:: ስለዚህም ተዓማኒነቷ ለፓርቲዋ ወይንም ፓርላማው ውስጥ ላሉት ወኪሎች ብቻ ነው:: አጠቃላይ ማህበረሰቡን በእኩልነት ለማገልገል የገባችው ቃል ወይንም እንዴት ሁሉንም ማህበረሰብ እንደምታገለግል በዝርዝር ያስቀመጠችው ፕሮግራም (ካጠቃላይ የፓርቲው ፕሮግራም ውጭ) የላትም:: የስልጣኗ መሰረትም መላው (ወይንም አብዛኛው) ህዝብ አይደለም:: ይህ ሁኔታ እንደኛ አገር የዘውጌ ማንነት በበረታበት ሁኔታ ሀገራዊ ማንነትን የሚያጠናክርበት መንገድ የለውም:: በመላው ህዝብ የተመረጠች ፕሬዜዳንት በምትኖርበት ሁኔታ ግን በመጀመሪያ ተመራጯ ለምን ሥልጣን እየተወዳደረች እንደሆነ መላው ማህበረሰብ ያውቃል:: ህዝቡ የሚመርጠውም ለዚያ ሥልጣን ብቁ ነች አይደለችም ብሎና በዚያ መስፈርት መዝኖ ነው::[2] ሁለተኛ እንደ ኢትዮጵያ ባለ ሀገር በብዙሀኑ ህዝብ ለመመረጥ የተለያዩ ዘውጌ ማህበረሰቦችን ድጋፍ ይፈልጋል:: የአንድ ዘውጌ ማህበረሰብን ጥቅም ብቻ የሚያስጠብቅ ነው ከተባለ ብዙሀኑ ሊመርጠው አይችልም:: ስለዚህም ፕሬዜዳንት የመሆን ፍላጎት ያለው ሰው ሀገሪቱን ከዘውጌዎች በላይ በሆነ ማንነት የማሰባሰብ ወይም ቢያንስ ለአንድ ዘውግ የሚያደላ አይደለም ተብሎ መታመን አለበት:: የፕሬዜዳንቱን ዕጩ የሚያቀርበው ፓርቲው እንኳን ቢሆን ፓርቲው ለፕሬዜዳንትነት የሚያቀርበው ዕጩ በመላው ሕዝብ ዘንድ ኢአድሏዊ በመሆኑ የሚታወቅ መሆኑን ከግምት ማስገባት አለበት:: ይህም በፓርቲው ውስጥም እንኳን የፖለቲካ ሥልጣን ይገባኛል የሚል ታታሪነት (ambition) ያላቸው ግለሰቦች ዘውጌያዊ ስሜታቸውን እንዲሞርዱ፤ ብሎም በሀገር ደረጃ እንዲያስቡ ያደርጋቸዋል:: ይህ ደግሞ ባንዴም ባይሆን በሂደት የፖለቲካ ፍላጎትና ታታሪነት ያላቸውን ሰዎች ገና ከመነሻው ከዘውግ ባሻገር እንዲያስቡ ያበረታታቸዋል የሚል እምነት አለኝ:: ይህ ደግሞ እየተጠናከረ ሲሄድ ሀገራዊ ማንነትንም እያጠናከረ ይሄዳል የሚል እምነት አለኝ::
ከዚህ ጉዳይ ጋር በተያያዘ የሚነሳው አንድ አስፈላጊ ጉዳይና የሥርዓቱን ቅርጽ የሚወስነው ጉዳይ ለሥራ አስፈጻሚነት የሚመረጠው ፕሬዜዳንት በምንም ሁኔታ ከ50% በላይ የሆነውን ህዝብ ይሁንታ ያገኘ መሆኑን ማረጋገጥ ነው:: እንደሚታወቀው በጀማሪ ዴሞክራሲያዊ ሥርዓቶች የሚታወቀው አንድ ነገር ቢኖር ሥልጣን ላይ ለመውጣት ፍላጎቱና ታታሪነቱ ያላቸው ሰዎች እጥረት አለመኖሩ ነው:: በዚህ ሁኔታ ለምርጫ በእጩነት የሚቀርቡት ሰዎች ቁጥራቸው የበዛ ሊሆን ይችላል:: የዘውግ ክፍፍሉ መስመር ይዞ ጠንካራ አገራዊ ማንነት እስከሚገነባ ድረስም ለእጩነት የሚቀርቡት ሰዎች የተወሰነ የዘውግ ድጋፍ የሚያገኙ ሊሆኑ ይችላሉ:: በዚህ ጊዜ በአንድ ዙር ምርጫ ከሌላው በዛ ያለ ድምጽ ያገኘ እጩ የሚመረጥበት ሁኔታ ካለ የብዙሀኑ ድምጽ ሳያስፈልገው ምርጫውን ባብላጫ ድምጽ ብቻ የሚያሸንፍ ሊኖር ይችላል:: ይህ ደግሞ ከላይ የጠቀስኩትን የፕሬዜዳንቱን የሀገር መሪ የመሆን ተቀባይነት በእጅጉ ያዳክመዋል፤ የዘውጌ ክፍፍሉንም የበለጠ ሊያጠናክረው ይችላል:: ስለዚህ አንዱ በግልጽ መቀመጥ ያለበት ነገር በመጀመሪያ ዙር ምርጫ 50% በላይ ያገኘ እጩ ከሌለ ከፍተኛውን ድምጽ ያገኙት ሁለት እጩዎች እንደገና ለውድድር ቀርበው ከሁለቱ ከ50% በላይ ያገኘው እጩ የሚያሸንፍበትን ሂደት መከተል ያለብን ይመስለኛል:: ይህ ባንድ በኩል ከስልጣን ፍላጎት ባሻገር ለቢሮው የሚመጥን ምንም ይህ ነው የሚባል ችሎታም ሆነ ህዝባዊ ተቀባይነት የሌላቸውን ሰዎች በምርጫው ውስጥ ገብተው የውድድሩን ሂደት መጫወቻ እንዳያደርጉት ከወዲሁ ተስፋ የሚያስቆርጣቸው ሲሆን በዋናነት ግን ከላይ እንደጠቀስኩት ያለ ብዙሀኑ ድምጽ ይሁንታ በጎንዮሽ ድርድርና አሻጥር የሚገኝ ሥልጣን እንደማይኖር ምልክት ይሰጣል::
ይህን ጉዳይ በመጠኑ ያነሳሁበት ምክንያት ግልጽ ከሆነ ይበልጥ አከራካሪ ሊሆን ስለሚችለው የመጀመሪያውን ምርጫ በሚመለከት ያለኝን ሀሳብ አቅርቤ ላጠቃልል::
ለ) በሽግግሩ ወቅት ማህበረሰቡን ለቋሚው ሥርዓት የሚያዘጋጁና የማህበረሰቡን ስነልቦናዊ ድባብ የሚያዘጋጁ ሥራዎች
ሌላውና ከመጀመሪያው ባልተናነሰ አጽንኦት ተሰጥቶት የሚሰራበት የሽግግር ወቅት ስራ በሽግግሩ ሙሉ ዘመን በማህበረሰቡ ዘንድ እንዲፈጠር የሚፈለገውን የስነ ልቦና ድባብ የሚቀርጹ ስራዎች ናቸው:: እነኝህ ስራዎች ገሚሶቹ ከላይ በተጠቀሱት ተቋማት የሚሰሩ ሲሆኑ ሌሎቹ መንግሥት በሚሰራቸው ሳይሆን በማይሰራቸው፤ ማህበረሰቡ ውስጥ በሚኖሩ ወይንም ሽግግሩን ተከትሎ እንደ አዲስ በሚፈጠሩ የማህበረሰቡ ተቋማት የሚሰሩ ናቸው:: እነኝህን ተቋማት አንድ ሁለት ብሎ ከመጥቀስ ይልቅ በማህበረሰቡ ዘንድ እንዲፈጠር የሚፈለገውን ስነ ልቦናዊ ድባብ መግለጹና ለዚህም የሚያስፈልጉትን ሁኔታዎች ማስቀመጡ ይቀላል:: ባለፉት አርባ ግድም አመታት በኢትዮጵያ ሥልጣን የጨበጡ መንግሥታት በማህበረሰቡ ላይ ከፈጠሩት አስከፊ ሁኔታዎች ውስጥ አንዱና ዋናው የማህበረሰቡን ስነ ልቦና ማኮላሸትና የሞራል መሰረቱን መናድ ነው:: ይህንን የመጠገን ሂደት መጀመር የሽግግር ወቅቱ አንድ ሥራ ነው::
ያገዛዝ ስርዓቶች ለመግዛት ከሚያስፈልጋቸው ነገር አንዱ ህብረተሰቡን በፍርሀት ቆፈን ውስጥ መክተት ነው:: እየፈሩ ስለ ሀገር የልብን መናገርና መከራከር አይቻልም:: እየፈሩ በነጻነት መምረጥ አይቻልም:: እየፈሩ የመንግሥትንና የመንግሥት ባለሟላትን ስህተቶችና ጥፋቶች ማጋለጥ አይቻልም:: በፍርሀት ማህበረሰብ ውስጥ የዴሞክራሲያዊ ስርዓትን መሰረቶች መገንባት አይቻልም:: ስለዚህ በሽግግሩ ወቅት የመንግሥት (እንዲሁም ሌሎች ማህበራዊ ተቋማት) አንዱ ስራው ማህበረሰቡን ከዚህ የፍርሀት ቆፈን ማላቀቅ ነው:: እንደ ኢትዮጵያ ባሉ ሀገራት በአብዛኛው የፍርሀት ምንጭ መንግሥት ራሱ ነው:: ማህበረሰቡን ከፍርሀት ለማላቀቅ ቆርጦና አስቦ የሚሰራ መንግሥት፤ ማህበረሰቡ መንግሥትን እንዲፈራ ለረጅም ጊዜ የደረሰበትን የስነልቦና ተጽእኖ ገፍፎ በምትኩ መንግሥት የሚፈራ ሳይሆን በስራው የሚከበርበትን ሁኔታ መፍጠር አለበት:: በዚህ ዙሪያ መንግሥት ነጻ ውይይትን የሚያበረታታበት (የመንግሥት ሚዲያን በነጻነት እንዲሰራ በማድረግ)፤ ከመንግሥት ውጪ ሀላፊነት የሚሰማቸው ነጻ የህትመትም ሆነ የኤሌክትሮኒክ ሚዲያዎች በስፋት የሚሰራጩበትን ሁኔታ ማመቻቸት፤ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በነጻነት ምሁራዊ ውይይቶችን እንዲያዘጋጁ ማበረታታት፤ የተለያየ የፖለቲካ አመለካከት ያላቸው የፖለቲካ ሰዎችም ሆኑ ምሁራን እነኝህን ሚዲያዎች ተጠቅመው በሀገሪቱ ጉዳይ ላይ በድፍረት እንዲሳተፉ ማበረታታት፤ ማህበረሰቡ በያካባቢው በሀገሩ ጉዳይ ላይ ያለምንም ፍርሀት የሚሳተፍበትን ሁኔታዎች ማመቻቸት…ወዘተ በጣም አስፈላጊ ነው::
ከዚህ ጋር የተያያዘና የማህበረሰቡን ስነ ልቡና ሊያረጋጋ የሚችል ሌላ ሥራ የብሄራዊ እርቅ ሂደት ነው:: በደርግ ሥርዓትም ሆነ በወያኔ ያገዛዝ ዘመን ብዙ በጣም ብዙ ከፖለቲካ ጋር የተያያዙ ወንጀሎችና ግፎች ተፈጽመዋል:: ብዙ ኢትዮጵያውያን ሞተዋል፤ አካለ ስንኩላን ሆነዋል፤ ተሰደዋል ከኑሮ ተፈናቅለዋል:: እንደ ማህበረሰብ እነኝህ ኩነቶች የስነ ልቡና ጠባሳ ፈጥረዋል:: ብዙዎቹ በደሎች ገና ቁስላቸው ያላሻረ ነው:: ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት በተረጋጋ ሁኔታ እንዲጀመር ከተፈለገና ሥርዓቱ የሚፈልገው ቀና ማህበራዊ ውይይትና ክርክር እንዲኖር ካስፈለገ ይህ ያልደረቀ ቁስል የሚያሽርበት መንገድ መፈለግ አለበት:: ይህ በተበዳዮች በኩል ትልቅ ትዕግሥት፤ ሆደ ሰፊነት፤ ይቅር ባይነት፤ በበዳዮች በኩል ደግሞ እውነተኛ ጸጸት የሚጠይቅ አስቸጋሪ ስራ ነው:: ባንድ በኩል ላለፈው ፍትህ ፍለጋ: በሌላ በኩል የወደፊቱ የመረጋጋት ፍላጎት ማህበረሰቡን ወጥረው የሚይዙት አስቸጋሪና አስጨናቂ ተግባር ነው:: ይህ በምን መልክ ይደረጋል የሚለው በራሱ የሰከነ ውይይት የሚፈልግ ነው:: ግን በሽግግሩ ወቅት መተግበር ያለበት ሥራ ነው:: ማህበረሰቡን ከፍርሃት የማላቀቅና ባዲስ መንፈስ የማስጀመሩ ስራ አንድ አካል ነው::
ማህበረሰቡን የፍርሃት ቆፈን ውስጥ የሚከተው ግን መንግሥት የሚያደርገው ድርጊት ብቻ አይደለም:: የማህበረሰቡን ሰላምና ደህንነት የሚያውኩ ከመንግሥት ውጭ ያሉ ሀይሎችም ካሉ በማህብረሰቡ ስነልቦና ላይ ተመሳሳይ ተጽእኖ አላቸው:: ስለዚህ ማህበረሰቡን ከፍርሀት ቆፈን የማላቀቅ አንዱ የሽግግሩ መንግሥት ስራ በሀገሪቱ ሰላምን ማስፈን ነው:: በሃሳብ ደረጃ የሚደረጉ ውይይቶችና ክርክሮች ያለምንም ተጽእኖ እንዲስተናገዱ እያበረታቱ እነኝህ ክርክሮች በምንም አይነት ወደ ሀይልና “የማይስማማን አመለካከት በጉልበት የሚያፍን” ወይንም ምናልባት ለምርጫው ጊዜ ለመዘጋጀት ካሁኑ ተቀናቃኞችን የማኮላሸት አይነት አካሄድ እንዳይሻገሩ መጠበቅ በጣም ያስፈልጋል:: ይህ ብዙ ጊዜ የሚሆነው በፖለቲካ ድርጅቶችና ደጋፊዎቻቸው አካባቢ፤ በተለያዩ የሃይማኖት አክራሪ መሪዎችና ተከታዮች አካባቢ፤ የመንግሥትና የሚዲያ አይን በበቂ በሌለባቸው ቦታዎች፤ ባጠቃላይ ስሱ ስሜቶች በሚንጸባረቁባቸው ጉዳዮችና የመንግሥትን ሥልጣን ሀብት ለማካበት እንጠቀምበታለን ብለው የሚያስቡ የፖለቲካ ድዊዎች አካባቢ ስለሆነ የሽግግር መንግሥቱ የጫወታውን ሕግ ለሁሉም እኩልና ግልጽ አድርጎ ካስቀመጠና ለሕጉ ተዓማኒነቱን እራሱ በተግባር እያሳየ ለእንዲህ አይነት ግጭቶች ምንም ትዕግስት እንደሌለውና ፍጹም ተቀባይነት እንደማይኖራቸው ማሳየት አለበት:: በተቻለ መጠን የሚደረጉ ውይይቶችና ክርክሮች ከውሸት የጸዱ፤ ምክንያታዊና የሰለጠኑ እንዲሆኑ በምሳሌነት ማሳየትና መምራት አለበት::
ፍርሃትን ከማስወገድ በተጨማሪ የማህበረሰቡን የሞራል መሰረት የመገንባት ጅማሮ (ይህ ረጅም ጊዜ የሚወስድ ሥራ መሆኑን ባለመርሳት) ታስቦበት መሰራት የሚጀምረውም በዚህ የሽግግር ወቅት ነው:: እንደሚታወቀው በተለይ በወያኔ ሥርዓት እጅጉን የተጎዳው የማህበረሰቡ የሞራል መሰረት ነው:: ሥርዓቱ የህብረተሰቡን ግብረገብነት የሚቀርጹትን የሃይማኖት ተቋማት ከማራከሱ ባሻገር፤ የማንኛውም ህብረተሰብ ሰላምና ዘላቂነት ዋስትና የሆኑትን ማህበራዊ እሴቶች ሆን ብሎ ንዷቸዋል:: ለዓብነት ያክል ሁለት ምሳሌዎችን ብቻ እንጥቀስ:: ውሸትና ሙስና:: እነኝህ ሁለት ማህበራዊ ደዌዎች በማህበረሰባችን ዘንድ ቤታቸውን ሰርተዋል ማለት ይቻላል:: ያገዛዝ ስርዓቶች አይነተኛ መገለጫ የሆኑ፤ ውጤታቸው ግን ካገዛዝ ስርዓቱ ተጠቃሚዎችም ባለፈ የማህበረሰቡን ስነልቦና ሁሉ የሚበክልና የበከለ መሆኑን መካድ አይቻልም:: ስለዚህም እነኝህን ደዌዎች ለማከም ሰፋ ያለ የህብረተሰብ ተሳትፎን የሚጠይቅ ነው:: ይህንን ስራ ግን በተግባር በማሳየት ቀዳሚውን ሚና የሚጫወተው የሽግግሩ መንግሥት ነው:: ለምሳሌ የሽግግሩ መንግሥት ማህበረሰቡን ላለመዋሸት፤ የመንግሥት ባለሟላት በምንም አይነት አውቀው ውሸት እንዳይናገሩ፤ እንዲህ አይነት አስነዋሪ ምግባር በአድራጊዎቹ ላይ ከፍተኛ ዋጋ እንደሚያስከፍል ማሳየት ይችላል:: የስነ ጥበብ ባለሙያዎች የውሸትን ማህበራዊ ጉዳት በሚመለከት ማህበረሰቡን የሚያስተምሩ ብዙ የኪነት ስራዎች ሊሰሩ ይችላሉ:: ትምህርት ቤቶች ወጣቶችን በዚህ ዙሪያ ማስተማር ይችላሉ…ወዘተ. ሙስናንም በተመለከተ እንደዚሁ:: የሽግግሩ መንግሥት ከሙስና የጸዳ እንዲሆን፤ ማህበረሰቡን ሙስና “ተጎጂ የሌለበት በሽታ” (victimless) ሳይሆን ጠቅላላ ማህበረሰቡን በተለይ ግን ድሆች ዜጎችን የበለጠ የሚያጠቃ፤ የማህበረሰቡን የሞራል ህልውና፤ የፖለቲካ መረጋጋትና የሚፈጠረውን ሥርዓት ይዘት ለዘላቂው የሚበክልና ያለይቅርታና ርህራሄ መዋጋት ያለብን ተውሳክ መሆኑን ማስረዳት፤ በሙሰኞች ላይ በሀገር ውስጥም ሆነ በውጭ እየተከታተሉ ጠንካራ እርምጃ በመውሰድ በምንም አይነት በሙስና መክበር እንደማይቻል ማሳየት ይገባል:: መንግሥት እንዲህ አይነት ቆራጥ አቋም መያዙ ሲታይ በመንግሥት ባለሟሎች ዘንድ ብቻ ሳይሆን ባጠቃላይ በማህበረሰቡ ዘንድ የሚፈጠረው ስነልቦና ይህንን ነቀርሳ ለዘላቂው ለማስወገድ ትልቅ እርዳታ ይሰጣል:: በተለይ ከፖለቲካ ሥልጣን የሚገኝ የኢኮኖሚ ጥቅም አለ ብለው ፖለቲካውን ራሱን ለማቆሸሽ ወደኋላ የማይሉ አድርባዮችን ለመጥረግ፤ ስለዚህም ዴሞክራሲያዊ ሥርዓቱን በተሻለ የሞራል መደላደል ላይ ለማስቀመጥም ተጨማሪ እገዛ ያደርጋል:: እነኝህ በሽታዎች ባንድ ጊዜ ይነቀላሉ የሚል የዋህነት አይኖረንም:: ግን እውነተኛ ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ሲመሰረት የሚያስከፍሉት ኪሳራ ከፍተኛ መሆኑን በማሳየት በሽግግሩ ጊዜ የሚወሰዱት እርምጃዎች ለዘላቂ መፍትሄ መንገድ ይጠርጋሉ::
በሽግግሩ መንግሥት የስራ ዘመን የሚሰሩትን ስራዎች ለናሙና ያክል ካስቀመጥን የዚህ ውይይት ዋና ክፍል የሆነውንና የሽግግሩ ዘመን ማለቁንና ወደ ዘላቂው ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት የሚያሻግረንን፤ የመጀመሪያውን ዴሞክራሲያዊ ምርጫ በሚመለከት ያለኝን አመለካከት ከነመፍትሄው ወደሚገልጸው ክፍል እንሻገር::
የሽግግሩ ወቅት የመጨረሻና ወሳኝ ስራ፤ የመጀመሪያው ነጻና ፍትሃዊ ምርጫ
የሽግግሩ መንግሥት እነኝህን ሰፋፊ ስራዎች በብቃት መስራቱ ሳያንሰው ከምንም ነገር በላይ የብቃቱና የትክክለኛነቱ መለኪያ ስራውና በርግጥም ወደ ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት የመሸጋገሩን እውነታ የሚያበስረው ወይንም የሚሰብረው የመጀመሪያው ምርጫ ነጻና ፍትሃዊ፤ባገሪቱ ህዝብም ሆነ ባለማቀፉ ማህበረሰብ ዘንድ ተአማኒነት ያለው ምርጫ ማድረጉና ስልጣንን በሰላማዊ መንገድ ለተመራጩ ማስተላለፉ ላይ ነው:: ይህ ምርጫ ለዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታ ካለው ፋይዳ አኳያ ምናልባትም ሁሌም ከሚቀርቡት መፍትሄዎች ወጣ ያለና ደፋር (bold) መፍትሄ የሚፈልግ ሊሆን ይችላል:: መታወቅ ያለበት ዋናው ቁም ነገር ይህ ምርጫ እውነትም ነጻና ፍትሃዊ መሆኑ ላይ ብቻ አይደለም:: እውነተኛ የህዝብ ፍላጎት የተገለጸበት መሆኑን ምንም አይነት ጥርጣሬ እንዳይኖረው ማድረጉ ላይ ነው:: ነገሩን አስቸጋሪ የሚያደርገውም ይኸው ነው:: ከላይ እንዳልነው ማህበረሰባችን ባጠቃላይ፤ በተለይም የፖለቲካ ድርጅቶች አካባቢ ያለው ስር የሰደደ ጥርጣሬና አለመተማመን እስካለ ድረስ ሂደቱ ትክክል እንኳን ቢሆን በምርጫ በተሸነፉ ኃይሎች አካባቢ “ያላግባብ ነው የተሸነፍኩት” የሚል ስሜት (perception) መፈጠሩ የሚቀር አይመስልም:: በተለይ ደግሞ በሽግግሩ ወቅት የመንግሥት ሥልጣንን የያዘው ኃይል ምርጫውን እስካካሄደው ድረስና ይኸው ኃይል ምርጫውን ካሸነፈ የምርጫውን ሂደት ስለዚህም የሚፈጠረውን አዲስ ሥርዓት በጥርጣሬ ውስጥ ይጥለዋል:: ይህ ደግሞ ዘላቂ አደጋ ነው የሚሆነው:: ስለዚህ ይህን ምርጫ ከምንም አይነት ጥርጣሬ ነጻ ላማድረግ ምን መደረግ አለበት የሚለው ወሳኝ ጉዳይ ይሆናል::
ይህን ጥርጣሬ ፈጽሞ ለማስወገድ የሚቻለው ምርጫውን የሚያካሂደውን አካል በጊዜው ሥልጣን ላይ ካለው ኃይል ሙሉ ለሙሉ መለየት ነው:: ከዚያም በተጨማሪ ምርጫውን የሚያካሂደው ኃይል ይህን ምርጫ ለማካሄድ ብቃቱ ያለውና በሃገሪቱ ካሉት የፖለቲካ ኃይሎች ሁሉ ምንም ወገንተኛነት የሌለው መሆኑን ማረጋገጥ ብቻ ሳይሆን ይህንንው ለሁሉም የፖለቲካ ተቀናቃኞችና ነጻ ተመልካቾች ሁሉ ማሳመን ይጠበቅበታል:: የኢትዮጵያን ፖለቲካ በቅርብ ለሚከታተል ማንም ሰው ይህ ምን ያክል ከባድና ምስጋና የሌለው ሥራ እንደሆነ መገመት አያቅትም:: ታዲያ ይህንን ስራ ማን ቢሰራው ነው የተሻለ ተዓማኒነት የሚኖረው?
ይህን ጥያቄ ለመመለስ ያሉትን አማራጮች በጥንቃቄ መመልከትና ካሉት አማራጮች ውስጥ የበለጠ ከጥርጣሬ የጸዳ ነው የሚባለውን መምረጡ ተገቢነው:: ምርጫን ነጻና ፍትሃዊ ለማድረግ እስከዛሬ ከነበሩት ተመክሮዎች ውስጥ የሚከተሉት ይጠቀሳሉ:
ሀ) በመንግሥት በተቋቋመ ነጻ የምርጫ ኮሚሽን ዋና አስፈጻሚነት የሚካሄድ (በተጨማሪ የውጭ ታዛቢዎች ትዝብታቸውን የሚገልጹበት)
ለ) የሚቋቋመው የምርጫ ኮሚሽን በሃገሪቱ ከሚገኙት የፖለቲካ ድርጅቶች በእኩል ተዋጽኦ ማቋቋምና ኮሚሽኑ በምልዓተ ድምጽ የሚያሳልፈው ውሳኔ ትክክለኛ ነው ብሎ መቀበል
የመጀመሪያው አካሄድ ከሞላ ጎደል አብዛኛው ወደ ዴሞክራሲ የሚደረግ ሽግግር ተግባራዊ ያደረገው አካሄድና በኢትዮጵያም የተተገበረው ነው:: ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት መሰረት ያልጣለባቸው ሀገሮች ውስጥ ሁሌም ይህ አካሄድ በሥልጣን ላይ ያለው ኃይል የሚመርጠውና በብዙ ሃገሮች ተመክሮ እንደታየው በሥልጣን ላይ ያለው ኃይል እራሱን በሚጠቅም አኳኋን ሂደቱን ያጨናገፈበት ሁኔታ ነው የሚታየው:: ለዚህ ምሳሌ ከኢትዮጵያችን ውጪ ሌላ አገር መጥቀስ አያስፈልገንም:: በጣም በቅርብ የሆነ የሌላ ሃገር ምሳሌ ካስፈለገ ከሰሞኑ በግብጽ የሆነውንና በአፍጋኒስታን ባለፈው ዓመት የሆነውን ማየት ብቻ ይበቃል:: ይህ የሚሆንበት ምክንያት ደግሞ በሥልጣን ላይ ያለው ኃይል የምርጫ አስፈጻሚውን ሙሉ በሙሉ በቁጥጥር ስር በማድረጉ ብቻ ሳይሆን ከዚህ ጋር ተያይዞ የሚታየው የምርጫ አስፈጻሚው ኃይል ተቋማዊ ደካማነት ነው:: እንዲህ አይነት ተቋም በሕግ የተሰጠውን ነጻነት ተግባራዊ ለማድረግ ሶስት ተያያዥ ሁኔታዎች ተሟልተው መገኘት አለባቸው:: በመጀመሪያ የሕግ ተቋማቱ በራሳቸው ነጻ የሆኑና የመንግሥት ስልጣን የያዘውን አካል ከሕግ በታች መሆኑን ማስረገጥ የሚችሉ መሆን አለበት:: ይህ በራሱ ትልቅ ስራ ነው:: ቀጥሎ የምርጫ አስፈጻሚው ተቋም ራሱ ለነጻነቱ ቀናኢ የሆነ፤ ከምንም ነገር በላይ ለተቋሙ ነጻነት የቆመ፤ ሥራውንም በተገቢው ለመስራት የሚችል ተቋማዊ ብቃት ያለው መሆን አለበት:: ሶስተኛው ደግሞ በተቋሙ ውስጥ የሚሰሩ ሰራተኞች፤ በተለይ በሃላፊነት ላይ ያሉት ሰዎች፤ ከፍተኛ ሙያዊ ብቃት ያላቸው ብቻ ሳይሆን ሙያው የሚጠይቀው ጠንካራ መንፈስና የሞራል ልዕልና ያላቸው ሰዎች መሆን አለባቸው:: እንዲህ አይነት ተቋም እንዲኖር ደግሞ በሽግግር ወቅት ሥልጣን ላይ ያለው ኃይል የምር ፍላጎቱ ቢኖረው እንኳን፤ እንደ ኢትዮጵያ በፍርሃት ቆፈን ውስጥ ለረጅም ጊዜ ከቆየ ማህበረሰብ፤ ለዚህ የሚመጥን ክህሎትና ድፍረቱ ያላቸው ባለሙያዎች በአጭር የሽግግር ወቅት ይገኛሉ ማለት አስቸጋሪ ነው:: በሽግግሩ ባለስልጣናት የሚሾሙት የምርጫ ኮሚሽን አባላት ገና በቂ የሥራ ልምድና ተቋማዊ ነጻነት ባላዳበሩበት ሁኔታ የውጭ ታዛቢዎች መኖራቸው ይህንን ሁኔታ ሊቀይረው አይችልም:: የምርጫ ታዛቢዎች ምርጫው እንከን የለሽ ነው ቢሉ እንኳን ይህንን ውጤት ተሸናፊ ፖለቲከኞች በጸጋ ይቀበሉታል ማለት አይደለም:: ስለሆነም ይህ አማራጭ ከምንም አይነት ጥርጣሬ ውጪ የሆነና ፍጹም ተዓማኒነት ያለው ምርጫ ያካሂዳል ብሎ መገመት አስቸጋሪ ነው:: በተለይ በስልጣን ላይ ያለው ኃይል ይህን ምርጫ እስካሸነፈ ድረስ ጥርጣሬው በፍጹም የሚጠፋ አይሆንም::
ሁለተኛው አማራጭ በተለይ በምርጫ 97 ወቅት በምርጫው የተሳተፉ ተቃዋሚ የፖለቲካ ኃይሎች በአማራጭነት ያቀረቡት አካሄድ ነበር:: በምክንያትነት የቀረበው በምርጫ ቦርዱ የሚሳተፉት ሁሉም የፖለቲካ ሀይሎች እስከሆኑ ድረስ ሂደቱ ለማንም የፖለቲካ ኃይል በማያደላ መልኩ እንዲካሄድ ያደርጋሉ፤ ውጤቱንም ለመቀበል ያስችላቸዋል የሚል መከራከሪያ ነበር:: ይህ መከራከሪያ መሰረት ያደረገው ሁሉም የፖለቲካ ኃይሎች ነጻና ፍትሃዊ ምርጫን ይፈልጋሉ፤ ከዚህም ተጠቃሚ ናቸው የሚለው እሳቤ ነው:: ይህ ግን ሁሌም እውነት ነው ማለት አይቻልም:: ለውሳኔ በሚቀርብላቸው ጉዳዮች ላይ በቀረቡት ማስረጃዎች ፋይዳ ሁሉም ባይስማሙስ? በድምጽ ብልጫ ይወስኑ ካልን በድምጽ የተሸነፉት የፖለቲካ ሃይሎች ተወካዮች ያሸነፉትን ሁሉ “ምርጫውን አጭበረበሩ” ብለው ላለመክሰስ ምን ይከለክላቸዋል? ይህንንስ የሚያደርጉ ከሆነ (ምንም እንኳን ክሳቸው ውኃ የማይቋጥር ቢሆን) ደጋፊዎቻቸውንና በምርጫው ውጤት ያልተደሰተውን ሁሉ በምርጫው ተዓማኒነት ላይ ጥርጣሬ እንዲኖር ስለዚህም ስሜት በማነሳሳት ወደ ግጭት እንዲሄድ አያደርጉም ወይ? ለዚህ ምንም ማረጋገጫ የለም:: የኢትዮጵያን የፖለቲካ ሃይሎች ስብጥር በደንብ ለሚያውቅ ግን ይህ አይሆንም ብሎ ሊምል አይችልም:: ይህ ሞዴል ግን ከዚህም ያለፈ ያሰራር ችግር ሊገጥመው ይችላል:: የተለያየ የፖለቲካ አመለካከት ያላቸው በመሰረታዊ መንገድ የማይተማመኑ ኃይሎች ባንድ ላይ ሆነው በየጊዜው በሚያደርጉት መጓተት የምርጫ አስፈጻሚው አካል በእርግጥም የተቀላጠፈና ብቃት ያለው ሥራ መስራት ይችላል ወይ የሚለውን ጥያቄ በአወንታዊነት መመለስ አይቻልም:: ይልቁንም ኮሚሽኑ ራሱ የግጭት አመንጪ ሊሆን የሚችልበት እድሉ የሰፋ ነው::
በነኝህና ተመሳሳይ ምክንያቶች እነኝህ ሁለቱም የተለመዱ ሞዴሎች በተለይ አሁን ባገራችን የፖለቲካ ሃይሎች ዘንድ ያለውን አለመተማመን ሊያከስም የሚችል ተቀባይነት ያለው ወደ ተረጋጋ ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት የሚያሻግር ምርጫ ሊደረግ ይችላል የሚል እምነት የለኘም:: ስለዚህ ከነኝህ ከተለመዱ አካሄዶች ወጣ ያሉና ያልተለመዱ ደፋር አካሄዶችን መቃኘቱ ይጠቅማል:: ከዚህ አንጻር ሁለት አማራጮችን በጥንቃቄ መመልከቱ ይበጃል እነኝህም:
በሽግግሩ ወቅት በሥልጣን ላይ ያሉ ኃይሎች ወይንም በሽግግሩ መንግሥት ውስጥ ተሳታፊ የሆኑት ኃይሎች በመጀመሪያው ምርጫ ላይ እንዳይሳተፉ ማድረግ
የመጀመሪያውን ምርጫ ምንም ኢትዮጵያዊ ኃይል ሳይኖርበት ምርጫ የማካሄድ ልምድ፤ ክህሎትና፤ ገለልተኛነት ያለው የውጭ ሀገር መንግሥት ወይንም መንግሥታዊ ያልሆነ ተቋም በሙሉ ሥልጣን እንዲያካሂደው መስማማት::
እነኝህን ሁለት ያልተለመዱ አማራጮች ከነ አወንታዊና አሉታዊ መከራከሪያቸው አቅርቤ በእኔ እምነት የተሻለውን በመምረጥ ይህንን ውይይት ላጠቃል::
የመጀመሪያው አማራጭ ጠንካራ ጎኖች ያሉትን ያክል ተግባራዊነቱን የሚያሰናክሉ ደካማ ጎኖች አሉት:: ከጠንካራ ጎኖቹ ውስጥ ምናልባት ዋናው በሽግግሩ ወቅት ስልጣን ላይ ያሉ ኃይሎች በመጀመሪያው ምርጫ ላይ ምንም ቀጥተኛ የሆነ የራስ ጥቅም ከሌላቸው (በምርጫው ስለማይሳተፉ) ምርጫውን ያለምንም ወገንተኛነት ለማካሄድ ይችላሉ የሚለው ነው:: በዚህ ሁኔታ የሽግግሩን ስልጣን የያዙ ሰዎችን ወይንም የፖለቲካ ቡድኖችን የሚገፋፋቸው ወይንም የሚያገኙት ጥቅም (incentive) የዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ሲፈጠር የማየት ፍላጎት ነው ማለት ነው:: ይህ ከሆነ ደግሞ ምርጫውን ያለወገንተኛነት ከማካሄድም በላይ በሽግግሩ ወቅት መሰራት ያለባቸውን ከላይ የዘረዘርናቸውን ስራዎች በብቃትና በንጽህና የመስራት ፍላጎታቸው ከፍተኛ ይሆናል ብሎ መጠበቅ ይቻላል:: ሌላው የዚህ አማራጭ በጎ ጎን በሽግግሩ ሂደት ማን ይሳተፍ የሚለውና የብዙ መጓተት ምክንያት የሆነውን የውስጥ ፍላጎትና ግፊት፤ ስለዚህም በፖለቲካ ኃይሎች መሀከል ያለውን ጥርጣሬና አለመተማመን፤ ይቀንሰዋል የሚል ነው:: ቀደም ብዬ እንደጠቀስኩት በሽግግሩ ላይ መሳተፍ ለዘላቂው ስልጣን መወጣጫ ይሆናል ብለው የሚያስቡና የሚጓጉ ኃይሎች በሽግግር መንግሥቱ መሳተፍ እንዲያውም ከዘላቂው ሥልጣን የሚያቅብ መሆኑን ሲያውቁ በሽግግሩ ወቅት ባለ ስልጣን የመሳተፍ ፍላጎታቸውን ያቆሽበዋል[3]፤ ይህ ደግሞ የሽግግሩ ሥራ ንጹህ የመሆኑን እድል በዚያው ልክ ያሰፋዋል:: ከዚህ ጋር የተያያዘው ሌላው ጥቅም ደግሞ ከሽግግሩ በኋላ በምርጫ በስልጣን ላይ የሚወጣው መንግሥት የሽግግሩን ሥልጣን ከያዘው የተለየ እንደሚሆን ከወዲሁ ከታወቀ፤ የሽግግሩን ስልጣን የያዙት ኃይሎች ወደፊት ከሚመጣ ተጠያቂነት ራሳቸውን ነጻ ለማድረግ ጠንክረው ይሰራሉ፤ ስለዚህም ሽግግሩን ተአማኒ ብቻ ሳይሆን በሽግግሩ ወቅት የሚፈጠሩት ተቋማት በእርግጥም ከመጪው መንግሥት ስራ አስፈጻሚ ኃይል ነጻ ሆነው እንዲሰሩ የማድረግ እድላቸው የሰፋ ይሆናል የሚል ነው::
ባንጻሩ ይህ አካሄድ የራሱ የሆኑ ችግሮች አሉበት:: የመጀመሪያው የወያኔን መውደቅ እውን ያደረጉት ሃይሎችና የወደቀበት መንገድ ሳይታወቅ በጥቅሉ ይህን አማራጭ ለውጡን ያመጡት ሃይሎች በሙሉ ልብ ይቀበሉታል ለማለት አይቻልም:: ከዚያም በላይ ግን ወያኔን በመጣል ሂደት ትልቅ አስተዋጽኦ ያደረጉና ለዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ምስረታ ጠንካራ ፍላጎትና ራዕይ አለን ብለው የታገሉ ኃይሎችን ሥርዓቱን ለመፍጠር በሚደረግ ምርጫ መሳተፍ አትችሉም የሚል ስምምነት ማስቀመጥ የነሱን መብት መጋፋት ብቻ ሳይሆን ሃገሪቱንም ጠንካራና የዴሞክራሲ ወገንተኛ የሆኑ መሪዎች ሊያሳጣት ይችላል:: ህዝቡንም የሚፈልገውን እንዳይመርጥ ማእቀብ ያደርግበታል:: ከዚህ በተጨማሪ ግን በሽግግሩ ወቅት የመንግሥት ስልጣን የያዙ ኃይሎች እራሳቸው እንኳን በምርጫው ባይወዳደሩ ከሚወዳደሩት መሀከል በአንድ ምክንያት ወይንም በሌላ ለሚመርጡት ኃይል አያደሉም ብሎ አፍን ሞልቶ ለመናገር ይከብዳል:: የምርጫ ኮሚሽኑ ጠንካራና በእውነትም ነጻ እስካልሆነ ድረስ በጊዜው በስልጣን ላይ ያለው ኃይል ስለማይወዳደር ብቻ ምርጫው ተዓማኒ ይሆናል ማለት አይቻልም::[4] ስለዚህ ይህ አማራጭ ቀደም ብለው ከተቀመጡትና በተለምዶ ከሚሰራባቸው ሞዴሎች የተሻለ ተዓማኒ የመሆን እድል ያለው ቢሆንም በውስጡ ያዘላቸው ድክመቶች በቀላሉ የሚታለፉ አይደሉም:: ተግባራዊነቱም ለውጡን ባመጡት ኃይሎች መልካም ፍላጎት ላይ ብቻ የተመሰረተ ይሆናል::
የመጨረሻውና በእኔ እይታ ከሁሉም የተሻለ አማራጭ ነው ብዬ የማምነው የመጀመሪያውን ምናልባትም ሁለተኛውን ጨምሮ (ሰላማዊ የስልጣን ሽግግር እስከሚደረግ ድረስ) ምርጫውን ከሁሉም በሃገሪቱ ካሉ የፖለቲካ ኃይሎች ፍጹም ገለልተኛ በሆነ ሶስተኛ ሀገር ወይንም የሶስተኛ ሀገር ነጻ ተቋም እንዲደረግ ማድረግ ነው:: ይህ ሶስተኛ ሀገር በተቻለ መጠን እንደሀገር የተለየ ጥቅም (ጂኦ ፖለቲካዊ) ያለው መሆን የለበትም:: በገለልተኛነቱና በለዘብተኛነቱ የታወቀ፤ ለዴሞክራሲያዊ ሥርዓትና ለሰብዓዊ መብቶች መከበር ወገንተኛ መሆኑ ባለማቀፍ ደረጃ ብቻ ሳይሆን እስካሁን ከኢትዮጵያ ጋር ባለው ግንኙነት ያስመሰከረ፤ በሀገሪቱ ያሉትን የፖለቲካ ኃይሎች የማይጎረብጥ ሀገር መሆን ይኖርበታል[5]:: ይህ አማራጭ ዴሞክራሲያዊ ሥርዓትን በጥሩ ምሶሶ ላይ ለማቆም ብዙ ጥቅሞች ያሉት ሲሆን ምናልባት ሊያከራክር የሚችሉ አንድ ሁለት ድክመቶች ይኖሩታል:: ከድክመቶቹ እንጀምር:: እንዲህ አይነቱን አማራጭ የሚቃወሙ ሰዎች ሊያነሱ የሚችሉት አንድ መከራከሪያ እንዲህ አይነቱን ወሳኝ ሀገራዊ ስራ ለውጭ ኃይሎች መስጠት የሀገሪቱን ሉአላዊነት የሚነካ ምናልባትም የሀገሪቱን ክብር የሚያጎድፍ ሊሆን ይችላል የሚል መከራከሪያ ነው:: ይህ ግን በእርግጥም ክብረ ነክ ነው ቢባል እንኳን (እውነተኛ ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ባለመፈጠሩ በሀገሪቱ ላይ የደረሰውና እየደረሰ ያለው ውርደት ከዚህ በጣም የከፋ ነው) ከሚሰጠው ጥቅም ጋር አብሮ ቢመዘን ያን ያክል ጠንካራ መከራከሪያ ነው ለማለት ያስቸግራል:: ሌላውና ምናልባትም የበለጠ ሊታሰብበት የሚገባው (ከዚህ በፊትም እኛ እስከምናውቀው ድረስ በተግባር ታይቶ ስለማይታወቅ) እንዲህ አይነቱን ሀላፊነት ለመውሰድ የሚፈልግ ገለልተኛ ሀገር ወይንም ተቋም ይኖራል ወይ? ከተገኘስ ወጪውን ማን ይችለዋል? የሚለው ነው:: ይህ ግን በሀገሪቱ ያሉት ሁሉም የፖለቲካ ሃይሎች (በሽግግር መንግሥት ስልጣን ላይ ያለው ኃይል ተጨምሮ) እስከተስማሙበት ድረስ እንዲህ አይነት የዴሞክራሲ ወገንተኛ መንግሥት ማግኘትና ይህም መንግሥት ወጪውን በእርዳታ መልክ ለመሸፈን ያስቸግረዋል ለማለት አይቻልም:: ይህን ውይይት ከዳር ለማድረስ ግን እንዲህ አይነት አካል ይገኛል በሚል እሳቤ የአማራጩን ጠንካራ ጎኖች እንመልከት::
በመጀመሪያ ብዙም ጥያቄ ውስጥ የማይገባው የእንዲህ አይነት ሃይል ገለልተኛነት ነው:: በሃገሪቱ ካሉት ኃይሎች ውስጥ አንዱ ወይንም ሌላው ቢያሸንፍ የሚያገኘው የተለየ ጥቅም ወይንም ጉዳት አይኖርም:: ይልቁንም የሃገሩ ወይንም የተቋሙ ታዋቂነትና ክህሎት (reputation) የሚመዘነው ምርጫውን በብቃትና በፍጹም ገለልተኛነት ማድረጉ ላይ ስለሆነ ለዚህ ጉዳይ አጽንኦት ሰጥቶ ይሰራል ተብሎ ይታሰባል:: ይህን ሃላፊነት የወሰደው ሃገር ይህ ስራ በብቃት መሰራቱን ማረጋገጥ ስላለበት (በምሳሌነትም በሌሎች ሃገሮች በአትኩሮት ስለሚታይ) በስራው ሰፊ ልምድ ያላቸውን ባለሙያዎች ለስራው ያሰማራል ተብሎ ይጠበቃል:: በዚህ ሂደት ላይ እንዲህ አይነቱ ኃይል ወደፊት የሚካሄዱትን ምርጫዎች የሚመራውን ቋሚ የምርጫ ተቋም የመገንባትም ሃላፊነት አብሮ ከወሰደ ለወደፊቱም ጠንካራና ነጻ ተቋም የመገንባቱን ስራ በጣም ያግዘዋል:: በእንዲህ አይነት ፍጹም ገለልተኛ ሃይል የተካሄደ ምርጫ ተአማኒነት በሃገር ውስጥም ሆነ ባለማቀፍ ደረጃ ጠንካራ ነው የሚሆነው:: እንዲህ አይነት ጠንካራና ተዓማኒ ኃይል ይህን አስቸጋሪ ሥራ ከሽግግር መንግስቱ ጫንቃ ላይ ካነሳለት የሽግግር መንግስቱ ከላይ የጠቀስናቸውን እጅግ አስፈላጊና አድካሚ ስራዎች ላይ ሙሉ ኃይሉን ስለሚያሳርፍ እነኝህን የሽግግር ጊዜ ስራዎች በተሻለ ብቃት የመወጣት እድሉም ከፍተኛ ይሆናል:: የሽግግር መንግሥቱም ለዘላቂ ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት መመስረት ያለውን ቁርጠኛነት በዚህ ፍላጎቱ ብቻ በሀገሪቱ ላሉት የፖለቲካ ኃይሎችም ሆነ ለመላው ማህበረሰብ ግልጽ ያደርጋል:: ይህ ደግሞ በማህበረሰቡ ስነልቦና ላይ የሚኖረው አወንታዊ እንድምታ በቀላሉ የሚታይ አይደለም::
የዚህ አማራጭ ጥቅም ግን ከዚህም በላይ አሁን እየተካሄደ ያለውንም የዴሞክራሲ ትግል በማገዝ ላይም ነው:: ይህንን ውይይት ስጀምር በተቃዋሚ የፖለቲካ ኃይሎች መሀከል ይህንን ሥርዓት ለማስወገድ ፍላጎት እያለም ለምን መተባበር አልተቻለም? የሚለውን ጥያቄ በጥቅሉ የመለስኩት በተለይ ሽግግሩን በሚመለከት ባለው የመተማመን እጦት እንደሆነ ጠቁሜ ነበር:: ይህንን አማራጭ በሃገሪቱ ያሉ የፖለቲካ ኃይሎች ቢወያዩበትና ቢቀበሉት፤ በውስጣቸው ያለውን ከፍተኛ የጥርጣሬ ዳመና ምን ያክል ሊገፈው እንደሚችል ለመገመት አያስቸግርም:: ከዚህም በላይ ግን የፖለቲካ ሥልጣን በህዝብ ፍላጎትና ውክልና ሳይሆን ባቋራጭ በሚደረግ መደራደር ይገኛል ብለው የሚያምኑ የፖለቲካ ደካሞችን ከመድረኩ በማጥራት በኩልም ትልቅ አስተዋጽኦ ይኖረዋል የሚል እምነት አለኝ:: በተለይም ደግሞ ወያኔ በጉልበት እንጂ በፍላጎቱ ስልጣን አይለቅም ብለው ነፍጥ አንስተው የሚታገሉ ኃይሎች እንዲህ አይነቱን አማራጭ በግልጽ ቢቀበሉት በትግሉ ሂደት እነሱ ስልጣን ከያዙ አይለቁም በሚል ፍርሃት በጥርጣሬ የሚያዩዋቸውንና በዚህም ምክንያት ትግላቸውን ከመደገፍ የሚታቀቡ ኃይሎችን ትግሉን እንዲደግፉ ማበረታታት ይችላል:: በሀገር ውስጥ በሚደረግ እንቅስቃሴ ከወያኔ ጋር በሚደረግ የምርጫ ሂደት ወያኔን ማባረር እንደማይቻል እያወቁም በሂደቱ የሚሳተፉ ሀይሎችም ከወያኔ የውሸት ምርጫ የተለየ ሰላማዊ አማራጭ በማቅረብ ማህበረሰቡን ለትግል ለማሰባሰብ፤ በወያኔ ላይም ከፍተኛ የሞራል ድል እንዲያገኙ ይረዳቸዋል:: ከሁሉም በላይ ግን ሰላማዊም ሆነ የአመጽ ትግል ለማድረግ የሚያስችል ከፍተኛ የሆነ የህዝብ የትግል መንፈስ ለማዳበር ይጠቅማል::
ማጠቃለያ: ወያኔን ለመጣል ጉልበት ያስፈልጋል የሚሉ ኃይሎች ይህን ሀሳብ ለምን እንዲደግፉት ይጠበቃል?
በዛሬ ጊዜ የሚደረግ፤ ከጉልበት ጋር የተያያዘ ትግል እንደቀድሞው የሚምል የሚገዘትበትና ለትክክለኛነቱ ምንም ጥርጣሬ የሌለው የኢኮኖሚ ወይንም ማህበራዊ ርዕዮተ አለም ይዞ የሚደረግ ትግል አይደለም:: ነፍጥ ያነሱ ኃይሎች ወደዚያ የተገፉት ሌላ አማራጭ በማጣት ነው:: ሁሉም የሚስማሙበት አንድ ዋና አላማ ቢኖር (ቢያንስ በፕሮግራማቸው ላይ ያስቀመጡት) ከምንም ነገር በላይ በኢትዮጵያ ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ተመስርቶ ማየትን ነው:: ከዚህ አላማ ጋር የተያያዘውና የዚህ ትግል ስኬት አንዱ ወሳኝ ጉዳይ በማህበረሰባችን ዘንድ የዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታ ሂደትን በሚመለከት የጠራ አመለካከት እንዲያዝ፤ በትግሉ ሂደት ደግሞ በሚፈጠረው ሥርዓት ዙሪያ ሰፋ ያለ ማህበራዊ መሰባሰብንና ፍላጎትን መፍጠር ነው:: ይህን ለማድርግ ለእንዲህ አይነቱ ሰፊ ማህበራዊ መሰባሰብ እንቅፋት ይሆናሉ ተብሎ የሚታሰቡ እክሎች እየተጠኑ የመፍትሄ ሃሳብ ማቅረብ፤ የተለያዩ የፖለቲካ ኃይሎችን በነዚህ መፍትሄዎች ዙሪያ ማወያየትና ይህን አመለካከት እንዲጋሩ በዚህም የትግሉ አካል እንዲሆኑ ማድረግ የታሰበው ውጤት ላይ ለመድረስ እጅግ አስፈላጊ ነው:: በዚህ የውይይት ሃሳብ ላይ የቀረበውን የመፍትሄ ሃሳብ በፖለቲካ ኃይሎችና በምሁራን ዘንድ መሸጥ ከተቻለ ትግሉን በማሳጠርም ሆነ በሚፈጠረው ሥርዓት ላይ የጠራ አመለካከት እንዲሁም ሰፋ ያለ የማህበረሰብ ድጋፍ (constituency for democracy) በመፍጠር ብሎም ሥርዓቱን እውን ለማድረግ የተጀመረውን ጉዞ ያሳካል የሚል እምነት አለኝ::
[1] ለዚህ ታሪካዊ ማስረጃ ካስፈለገ በአሁኑ ጊዜ በኢሕአዴግ ተቀርጾ የጸደቀውን ሕገ መንግስት በብዙ መልኩ የሚመስለውን በሶቭየት ሕብረት በእስታሊን አጋፋሪነት የጸደቀውን የ1936 ሕገ መንግሥት መመልከት ብቻ ይበቃል:: ይህ ሕገ መንግስት ብንመለከት በአንቀጽ 125 ላይ ያለምንም ሳንሱር የመጻፍ፤ የመናገር፤ የመሰብሰብ፤ የመደራጀት፤ ሰላማዊ ሰልፍ የማድረግ መብቶችን ያለምንም ገደብ ይፈቅዳል:: በአንቀጽ 134 ደግሞ ለሁሉም ላቅመ አዳም ለደረሰ ዜጋ በሚስጥር ድምጽ አሰጣጥ መሪዎቹን የመምረጥ መብት አልፎም በአንቀጽ 17 ደግሞ ማንኛውም የፌደሬሽኑ አካል የሆነ ክልል እራሱን የማስተዳደርና በሕዝብ ውሳኔ እስከመገንጠልና የራስን ሀገር እስከማቋቋም የደረሰ መብት ይሰጣል:: በተግባር የሆነውን ግን ሁላችንም የምናውቀው ነው::
[2] እንደሚታወቀው አንድ ሰው የመረጠውን አካባቢ ህዝብ ጥቅም የሚያስጠብቅ፤ ጥሩ ሕግ አውጪ ሊሆን ይችላል:: ይህ ማለት ግን ጥሩ ሀገራዊ መሪ ይሆናል ማለት አይደለም::
[3] ቆሸበ ማለት በእንግሊዘኛው supress the appetite የሚለውን ትርጉም የያዘ ነው::
[4] ባለፈው አመት በአፍጋኒስታን የታየው የምርጫ ቀውስ የቀድሞው ፕሬዜዳንት ካርዛይ በምርጫው ባይወዳደሩም እሳቸው የሚፈልጉትን ሰው ለማስመረጥ የምርጫ ኮሚሽኑን በመጠምዘዝ ኮሮጆ አስገልብጠዋል በሚል ነው:: በዚህም ምክንያት የምርጫ ኮሚሽኑ ሃላፊ ከስልጣናቸው ተነስተዋል::
[5] ከዚህ አንጻር የእስካንዲኔቪያ ሃገሮች ተመራጭ ይሆናሉ ብዬ አምናለሁ::

CategoryAmharic

ህወሓት በፈጠራቸው ድርጅቶች ውስጥ ተኩኖ ህወሓትን ማዳከም አርበኝነት ነው!


  • July 21, 2015
አርበኞች ግንቦት 7: የአንድነትና ዲሞክራሲ ንቅናቄ፣ ለኢህአዴግ እና አጋር ድርጅቶቹ አባላት የሚከተለው መልዕክት ማስተላለፍ  ይሻል።
def-thumbህወሓት ጥቂት አባላትና ደጋፊዎች ይዞ ታላቂቷን ኢትዮጵያ ለማንበርከክ እና ሀብቷን ለመመዝበር  እናንተን መጠቀሚያ ያደረጋችሁ መሆኑን የምታውቁት ነው። እናንተ አባል የሆናችሁባቸው ብአዴን፣ ኦህዴድ፣ ደህዴድ የተባሉ ድርጅቶች የራሳቸው ድርጅታዊ ነፃነት የሌላቸው የህወሓት አገልጋዮች መሆናቸው እነሱ ራሳቸው የሚነግሯችሁ ከመሆኑም በላይ እናንተም በዕለት ተዕለት ተግባራችሁ የምትታዘቡት ሀቅ ነው። እነዚህ ድርጅቶች ህወሓትን ለማስደሰት ሲሉ የራሳቸውን ሕዝብ የሚያስሩ፣ የሚገድሉ፣ የሚዘርፉ፣ ከቀየው የሚያፈናቅሉ፣ መኖሪያ ቤቱን የሚያስፈርሱ መሆናቸው እናንተም እየተሳተፋችሁበት ያለ ሥራ ነውና የምታውቁት ነው። “አጋር ድርጅቶች” የሚል ስያሜ የተሰጣችው  አብዴፓ፣ ቤጉህዴፓ፣ ጋህአዴን፣ ሀብሊ እና ኢሶዴፓ “አጋር” ሳይሆን የህወሓት ጀሌዎች መሆናቸው እናንተም እኛም የምናውቀው ነው። እናንተ አባል የሆናችሁባቸው ብአዴን፣ ኦህዴድ፣ ደህዴድ፣ አብዴፓ፣ ቤጉህዴፓ፣ ጋህአዴን፣ ሀብሊና ኢሶዴፓ  የተባሉ አድርባይ ድርጅቶች ባይኖሩ ኖሮ ህወሓት ለ24 ዓመታት ኢትዮጵያዊያን እየገደለና እያሰረ፤ እየዘረፈ በውሸት ምርጫና በውሸት ዲሞክራሲ ስም ፍጹም የሆነ ዘረኛ፣ ከፋፋይ፣ አምባገነናዊ ሥርዓት በመላው ኢትዮጵያ ውስጥ ሊያሰፍን ባልቻለም ነበር። ህወሓት በኢትዮጵያዊያን አናት ላይ እንዲፈነጭ እናንተ አባል የሆናችሁባቸው ድርጅቶች አስተዋጽዖ  ከፍተኛ  ነው።
ይህ ብቻም አይደለም። እናንተ አባል ሆናችሁ ድጋፍ ባታደርጉላቸው ኖሮ እነዚህ አድርባይ ድርጅቶች ባልኖሩም ነው። ስለሆነም ህወሓት በኢትዮጵያዊያን አናት ላይ እንዲፈነጭ፣ እናንተ ብቻ ሳትሆኑ ልጆቻችሁ እና የልጅ ልጆቻችሁ በሎሌነት እንዲያድጉ፤ ጥቂቶች በልጽገው ብዙሃኑ እንዲደኸዩ  እናንተ በግል አስተዋጽዖ አድርጋችኋል።
ብዙዎቻችሁ እነዚህ አድርባይ ድርጅቶችን የተቀላቀላችሁት በኑሮ ግዴታ፣ በትዕዛዝ፣ በአማራጭ እጦት ሰበብ፣ የሰብዓዊ ተፈጥሮችን አካል በሆነው የመንፈስ ደካማነት ምክንያት እንደሆነ፤ ድርጅታችሁ በሕዝብ ላይ የሚያደርሰው በደል እያያችሁ ህሊናችሁ እንደሚቆስል እናውቃለን። አንዳንዶቻችሁ ውስጣችሁ እያነባ እጆቻችሁ ኢፍትሀዊ ተግባር እንደሚፈጽሙ እናያለን። ኢህአዴግ እንደማፊያ ድርጅት መግባት እንጂ መውጣት የማይቻልበት ሆኖ እንዳገኛችሁት እናውቃለን። “ይህንን ድርጅት ከለቀቅኩ የሚጠብቀኝ እስር፣ አልያም ሥራ ማጣት ነው። ያኔ ምን ይውጠኛል? ትዳሬ፣ ልጆቼ፣ ወላጆቼ እንዴት ይሆናሉ?” የሚል ስጋት እንዳለባችሁ እንገነዘባለን። ህወሓትን በመርዳት ያቆማችሁት ሥርዓት እንኩዋንስ ለሌላው ለእናንተም ከፍርሃት ነፃ ሊያደርጋችሁ አለመቻሉን እናውቃለን። ድርጅታችን አርበኞች ግንቦት 7፣ እናንተ ያላችሁበት አጣብቂኝ ቀላል እንዳልሆነ ይገነዘባል። በዚህም ምክንያት ይህንን ጥሪ ለእናንተ ያቀርባል።
ሀገራዊና ሕዝባዊ ስሜት ያላችሁ፤ ለራሳችሁና ለቤተሰቦቻችሁ ክብር የምትጨነቁ፣ ለልጆቻችሁና ለልጅ ልጆቻችሁ ሎሌነትን  ሳይሆን ክብርን  ማውረስ የምትፈልጉ የኢህአዴግ እና የአጋር ድርጅቶቹ አባላት ሆይ! አባል የሆናችሁባቸውን ድርጅቶች ሳትለቁ፤ ኢህአዴግም ሆነ አጋር ድርጅቶቹ ውስጥ እያላችሁ ለህሊናችሁ፣ ለልጆቻችሁ፣ ለቤተሰቦቻችሁና ለሀገራችሁ የምትሠሩበት መንገድ ተመቻችቶላችኋልና ተጠቀሙበት።
የአገራችን የነፃነት ተጋድሎ ታሪክ እንደሚያስተምረን አርበኝነት ሁለት ዓይነት ነው። አንዱ በገሀድ፣ በግላጭ፣ በውጊያ ሜዳ የሚታይ አርበኝነት ሲሆን፣ ሌላው ደግሞ፣ በጠላት ጉያ ውስጥ ተኩኖ፣ ጠላትን መስሎ  የሚደረግ አርበኝነት ነው። ሁለተኛው ዓይነት አርበኝነት በተለምዶ  “የውስጥ አርበኝነት” ተብሎ የሚጠራ ሲሆን በተግባርና በውጤት ከአደባባይ አርበኝነት በምንም የማይተናነስ የጀግንነት ሥራ ነው። የውስጥ አርበኛ፣ አርበኛ ነው። የውስጥ አርበኛ ገድሉ  በታሪክ የሚወደስ፣ በአርዓያነቱ የሚጠቀስ የሀገሩ የቁርጥ ቀን ልጅ  ነው።
የኢህአዴግ አባላት ሆይ የውስጥ አርበኛ የመሆን እድላችሁን አታስመልጡ!
ዛሬ በምንገኝበት ሁኔታ የውስጥ አርበኝነት ማለት ብአዴን፣ ኦህዴድ፣ ደህዴድ፣ አብዴፓ፣ ቤጉህዴፓ፣ ጋህአዴን፣ ሀብሊ ወይም ኢሶዴፓ  ውስጥ ሆኖ ህወሓትን ማዳከም ማለት ነው። በእነዚህ ድርጅቶች ውስጥ ቀንደኛ የህወሓት ጉዳይ አስፈፃሚዎች እንዳሉ ይታወቃል። የውስጥ አርበኞች ተግባር እነዚህ ከህወሓት በላይ ህወሓት ሆነው እናንተ በወገናችሁ ላይ በደል እንትድፈጽሙ የሚያደርጓችሁ፤ ለህወሓት ባርነት መገዛትን መታደል እንደሆነ አድርገው የሚሰብኩ ቀንደኛ ባንዳዎችን መቆጣጠር ነው። የውስጥ አርበኛ ማለት በአምባገነን ሥርዓት ውስጥ ሆኖ ሥርዓቱ የሚያዳክሙ ተግባራትን የሚሠራ ጀግና ማለት ነው። የውስጥ አርበኛ ማለት በሕዝብ ላይ በደል የሚሠራን ሥርዓት በአሻጥር የሚያሽመደምድ ብልህ ዜጋ ማለት ነው። የውስጥ አርበኛ ማለት አለቆቹን እየሰለለ፣ ራሱ የተሳተፈበትም ቢሆን የሥርዓቱን እቅዶች ለታጋዮች አሳልፎ የሚሰጥ ባለውለታ ማለት ነው። የኢህአዴግና “የአጋር” ድርጅቶች አባላት በውስጥ አርበኝነት በመሳተፍ ለህሊናችሁ፣ ለልጆቻችሁና ለልጅ ልጆቻችሁ ውለታ መሥራት ትችላላችሁ።

የህወሓትን ዓላማ የማይደግፉ የህወሓት አባላት እንዳሉም እናውቃለን። ለእነሱም ህወሓት ውስጥ ሆኖ ህወሓትን ማዳከም ትልቅ የውስጥ አርበኝነት እንደሆነ ማስገንዘብ እንወዳለን። የፍትህ፣ የእኩልነት፣ የነፃነትና የዲሞክራሲ ጉዳይ ከዘር በላይ መሆኑ የሚረዱ፤ እነሱ ለራሳቸው እንዲሆን የሚፈልጉት ሌሎች ኢትዮጵያዊያንም የሚመኙት መሆኑን የተረዱ የህወሓት አባላት የኢፍትሃዊነት ምንጭ የሆነው ድርጅታቸውን በማዳከም ላይ የመልካም ዜግነት አክሊል መቀዳጀት ይችላሉ።
በህወሓትና ህወሓት የፈጠራቸው ድርጅቶች ውስጥ የምትገኙ ወገኖቻችን ፈልጋችሁ አግኙን፤ ደህንነታችሁ በተጠበቀ  መጠን በዘረኛ ድርጅት ውስጥ ሆናችሁ ዘረኝነትን፤ በፋሽስት ድርጅት ውስጥ ሆናችሁ ፋሺዝምን መዋጋትና ከህሊናችሁ ጋር ታርቃችሁ መኖር ትችላላችሁ። ይህን ስትሰሩ እኛ ከናንተ ጋር ነን። ይህንን ስትሠሩ እኛና እናንተ ለጋራ ዓላማ የምንሰራ ጓዶች  እንጂ ጠላቶች አንሆንም። ሥርዓቱን በማዳከም ረገድ የምትወስዱት ተጨባጭ እርምጃዎችን ማየት እንፈልጋለን። እኛን ማግኘት ከባድ አይደለም፤ ፈልጋችሁ አግኙን። ተባብረን አገራችን ከህወሓት  ፋሽስታዊ ዘረኛ አገዛዝ ነፃ  እናውጣ።

ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ!!!
CategoryEditorial

Sunday, 19 July 2015

ሊቀመንበራችን ትግል ሜዳ ውስጥ ነው!-መግለጫ


July 19, 2015
ሐምሌ 12 2007 ዓ.ም.
ህወሓት በኢትዮጵያዊያን እና በኢትዮጵያ ላይ ያሰፈነው ዘረኛና ፋሽስታዊ አገዛዝ እንዲያበቃ፤ በምትኩም ፍትህ፣ ነፃነት፣ እኩልነትና ዲሞክራሲ የሰፈኑበት የፓለቲካና የኢኮኖሚ ሥርዓት እንዲመሠረት እና የሀገራችን አንድነት በጠንካራ መሠረት ላይ ለማኖር አርበኞች ግንቦት 7: የአንድነትና ዲሞክራሲ ንቅናቄ ተገዶ የገባበት የመረረ የአመጽ ትግል መጀመሩን ይፋ ማድረጉ ይታወቃል። በዚህም መሠረት ኢትዮጵያዊያን የነፃነት አርበኞች በጀግነትና በጽናት እየታገሉ ነው።
ይህ ትግል በባርነትና በነፃነት መካከል የሚደረግ ወሳኝ ትግል ነው። የዚህ ትግል ውጤት የእኛ የዚህ ዘመን ትውልድ ሕይወት ብቻ ሳይሆን የአገራችንን የወደፊት ታሪክ፤ የልጅ ልጆቻችንን ሕይወት ይወስናል። በዚህም ምክንያት ይህንን ትግል በድል መወጣት ግዴታችን ነው። በዚህ ወሳኝ ወቅት ለነፃነት ግድ ያለው ኢትዮጵያዊ ሁሉ ከጎናችን ሊቆም ይገባል።
አርበኞች ግንቦት 7 አመራሩን ሁኔታዎች በፈቀዱ መጠን እና ትግሉ በሚጠይቀው ቦታ እንዲገኙ የሚያደርግ መሆኑ ሲገልጽ ቆይቷል። አሁን ትግሉ በደረሰበት ደረጃ የአመራሩ በትግሉ ሜዳ ውስጥ መገኘት አስፈላጊ መሆኑ ታምኖበት ሊቀመንበሩን ጨምሮ አመራሩን ወደ ትግሉ ሜዳ አንቀሳቅሷል። በዚህም መሠረት የንቅናቄው ሊቀመንበር ዶ/ር ብርሃኑ ነጋ ወደ ትግል ሜዳ ወርዷል።
ትግሉ መሯል። ወሳኝ የሆነ ትግል ውስጥ ገብተናል። የትግሉ መሪዎች የሕይወት መስዋዕትነት እሚከፈልበት ቦታ ይገኛሉ። በአሁኑ ሰዓት የንቅናቄው አመራር በተሟላ ሁኔታ በትግሉ ሜዳ ውስጥ እንዲገኝ ማድረግ ተችሏል። ኢትዮጵያዊያን እጅ ለእጅ ተያይዘን ዘረኛው የህወሓት አገዛዝን ከጫንቃችን ለማስወገድ ቆርጠን እንድንነሳ አርበኞች ግንቦት 7 ጥሪ ያደርጋል።
ኢትዮጵያን ከህወሓት አገዛዝ ነፃ የሚያወጣው አርበኞች ግንቦት 7 ብቻ አይደለም። ስለሆነም ከሌሎች ድርጅቶች ጋር የሚደረገው ትብብር ቀዳሚ ትኩረት ከተሰጣቸው ሥራዎች አንዱ ነው። አርበኞች ግንቦት 7 ከሌሎች ኢትዮጵያዊያን ድርጅቶች ጋር በመተባበር የተቀጣጠለው ሕዝባዊ አመጽ ለድል እንዲበቃ ይታገላል። ኢትዮጵያዊያንም በያሉበትም በተመሳሳይ ልዩነቶቻቸውን አቻችለው በህወሓት ፋሽስታዊ አገዛዝ ላይ ክንዳቸውን እንዲያነሱ አርበኞች ግንቦት 7 ጥሪ ያደርጋል።
እነሆ የአርበኞች ግንቦት 7 ሊቀመንበር ዶ/ር ብርሃኑ ነጋ በአካል ትግል ሜዳ ውስጥ ይገኛል። የሚችል ሁሉ እንዲከተል፤ መከተል የማይችል በያለበት ሁኖ ሁለገብ ትግሉን እንዲያጧጥፍ አርበኞች ግንቦት 7 ጥሪ ያደርጋል።
ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ!!!
አርበኞች ግንቦት 7 ለአንድነትና ዴሞክራሲ ንቅናቄ
CategoryAmharic

Monday, 6 July 2015

UN demands release of British activist jailed in Ethiopia amid torture fears – The Guardian


July 5, 2015
The Foreign Office has pushed for consular access to Andargachew Tsige with no tangible results, since the British citizen was abducted in Ethiopia a year ago
The UN has demanded the immediate release of a Briton held on death row in Ethiopia for more than a year, an intervention that campaigners say exposes Britain’s poor diplomacy towards the case.
Experts from the UN Human Rights Council have advised Ethiopia to pay Andargachew Tsige “adequate compensation” before sending him home to London, an abrupt hardening of its position on the case at a time when Britain pursues a softly, softly approach with no tangible reward.

Yemi Hailemariam campaigns in London to demand the immediate release of her partner, British citizen Andargachew Tsege, who has been held in Ethiopia since June 2014. Photograph: Alamy
Internal Foreign Office emails, disclosed for the first time, reveal that even before Tsige was kidnapped and jailed in an unknown location in June 2014, British officials had voiced fears at “the real risk of torture if [Tsige is] returned to Ethiopia”, along with “fair trial concerns”.
An eight-page judgment from the UNHRC’s working group on arbitrary detention handed to Ethiopia suggests such fears have been realised, saying that there is “reliable evidence on a possible situation of physical abuse and mistreatment which could amount to cruel, inhuman and degrading treatment.”
Tsige, 60, a father of three from London, and known to friends as Andy, was arrested in Yemen’s main airport while in transit and forcibly removed to the Ethiopian capital, Addis Ababa.
He is prominent in Ethiopian politics, having been leader of opposition party Ginbot 7, which has called for democracy, free elections and civil rights. The government has accused him of being a terrorist and in 2009 he was tried in his absence and sentenced to death.
Foreign secretary Philip Hammond has refused to demand his urgent release, preferring to push for consular access, a request rejected by Ethiopia. Tsige’s partner, Yemi Hailemariam, also a British national, who lives in London with their children, has spoken to him just once by telephone since his abduction.
Advertisement
Another internal government email from the UK ambassador to Ethiopia to Laurence Robertson MP, who heads the all-party parliamentary group on Ethiopia, describes the Ethiopians as “obdurate”.
Hammond recently attempted to harden up the UK’s position on Tsige, calling for rapid progress in the case, but campaigners say this remains significantly short of what is required. Another recent Foreign Office statement made no mention of Tsige, but welcomed the “generally peaceful environment” of the recent Ethiopian elections, which saw the government locking up political opponents and journalists.
Maya Foa, head of the death penalty team at legal charity Reprieve, said: “Despite the injustices that have been – and continue to be – committed against this British national, the foreign secretary refuses to ask for Andy’s release and his return back home to his family in Britain.
“The UN is right to be taking action and demanding Andy’s immediate release from his unlawful detention. The UK’s refusal to do the same is an unacceptable abdication of responsibility to one of its citizens.”
Kevin Laue of the human rights organisation Redress, which helps torture survivors, said: “The UK government should be outraged by this behaviour and should be responding in the strongest possible terms.” A Foreign Office spokesman said: “The foreign secretary has raised this case with the Ethiopian foreign minister on 13 separate occasions, most recently on 29 April 2015. The minister for Africa raised this again on 11 June. We will continue to lobby at all levels, conveying our concern over Andargachew Tsige being detained without regular consular visits and access to a lawyer.”
CategoryHuman Rights ...

Saturday, 4 July 2015

በህወሓት አገዛዝ እየተሰቃዩ ላሉ ወገኖቻችን ደህንነት የሚደረገው ዓለም አቀፍ ጫና ይቀጥል!


July 3, 2015
def-thumbከሣምንት በፊት የብሪታኒያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አቶ አንዳርጋቸው ጽጌን የሚመለከት አንድ መግለጫ አውጥቷል። በዚህ መግለጫው፣ አንዳርጋቸው ጽጌ ለአንድ ዓመት ሙሉ መሠረታዊ የሆኑ የታሳሪዎች መብት እንኳን ተነፍጎት ባልታወቀ እስር ቤት የሚገኝ መሆኑ እና በእንግሊዝ ባለሥልጣናትና በቤተሰቦቻቸው እንዲጠየቅ፣ ቋሚ የቆንስላና የህግ ምክር እንዲያገኝ በተደጋጋሚ የቀረበው ጥያቄ በወያኔ አገዛዝ ውድቅ መደረጉ በሁለቱ አገራት መካከል ያለው መልካም ግንኙነት የሚያሻክር መሆኑ ከወትሮው ጠንከር ባሉ ቃላት ገልጿል። አዲስ አበባ የሚገኘው የብሪታኒያ አምባሳደርም እንደዚሁ ከተለመደው ዲፕሎማሲያዊ ለስላሳነት ወጣ ያለ ያለ መግለጫ አዲስ አበባ ውስጥ ለሚታተመው ሪፓርተር ጋዜጣ ሰጥቷል። እነዚህ የሰሞኑ የእንግሊዝ መንግሥት መግለጫዎች በቀና የሚታዩ ቢሆንም የብሪታኒያ መንግሥት ማድረግ ይገባው ከነበረው እና ማድረግ ከሚችለው አንፃር ሲታይ ብዙ ይቀረዋል። የአውሮፓ ኅብረት የአቶ አንዳርጋቸው ጽጌ ጉዳይ በተደጋጋሚ አንስቷል። የተባበሩት መንግሥታትም የአቶ አንዳርጋቸው ጽጌ አያያዝ ጉዳይ ምርመራ እንዲደረግበት እንቅስቃሴ ጀምሯል። ከላይ የተዘረዘሩት ኩነቶች፣ በመላው ዓለም የሚገኙ ኢትዮጵያዊያን ያለሟቋረጥ የሚያደርጉት ውትወታ ውጤት እያመጣ መሆኑ ያሳያል። ይህ ጥረት ለወደፊቱም ተጠናክሮ መቀጠል ይኖርበታል።
በሌላ በኩል ደግሞ ኢትዮጵያ ውስጥ “አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ አስልጥኖ አሰማርቷችኋል” ተብለው እንደተለመደው በሀሰት የተከሰሱ ወገኖቻችን “አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ ኢትዮጵያ ውስጥ ስለሚገኙ መከላከያ ምስክር እንዲሆኑን ይታዘዝልን“ ብለው ሲጠይቁ ዳኛ ተብየው “የት እንደሚገኙ የማይታወቁ ሰውን በመከላከያ ምስክርነት ማቅረብ ይከብዳል” ብሎ ሲናገር ተደምጧል። አቶ አንዳርጋቸው ለምስክርነት ይቅረብ አይቅረብ ብይን ሊሰጥበት ቀጠሮ ተይዟል።
አርበኞች ግንቦት 7፡ የአንድነትና ዲሞክራሲ ንቅናቄ፣ የነፃነት አርበኛው የአቶ አንዳርጋቸው ጽጌ የእስር አያያዝ ሁኔታ ዓለም ዓቀፍ የዲፕሎማሲ አጀንዳ በሆነበት በዚህ ወቅት በህወሓት አገዛዝ በተሾመ ዳኛ “የት እንደሚገኙ የማይታወቁ” መባሉ አሳሳቢ ጉዳይ አድርጎ ይመለከተዋል። አርበኞች ግንቦት 7፣ በመላው ዓለም የሚገኙ ኢትዮጵያዊያን የተከሳሾች፣ የአቃቤ ህጉና የዳኛው ምልልስ ለተባበሩት መንግሥታት፣ ለአውሮፓ ኅብረትና ለእንግሊዝ መንግሥት እንዲደርስ እንዲያደርጉም ያሳስባል።
አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ ብቻ ሳይሆን በህወሓት እስርቤቶችና ከእስር ቤቶች ውጭ ባልታውቁ ቦታዎች ታስረው እየተሰቃዩ የሚገኙ ወገኖቻችን ሁሉ እና መላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ነፃ የሚወጣው፣ ኢትዮጵያዊያን በሚያደርጉት ሁለገብ ትግል ነው ብሎ አርበኞች ግንቦት 7 ያምናል። ስለሆነም ራሳችንን፣ ወገኖቻችንና አገራችን ነፃ ለማውጣት የምናደርገው ትግል ማጠናከር ግዴታችን ነው። እኛ ራሳችን እንጂ ማንም ነፃነታችንን አያጎናጽፈልንም።
ይህ እንዳለ ሆኖ ግን የህወሓትን እኩይ ተግባራት በዓለም አደባባዮች ማጋለጥ፤ የህወሓት አገዛዝን ወዳጅ ማሳጣት እና በእስር ላይ የሚገኙ ወገኖቻችንን ደህነት የሚያሻሽሉ ተጽዕኖዎችን መፍጠር እጅግ አስፈላጊ ተግባር በመሆኑ፣ በመላው ዓለም የሚገኙ ኢትዮጵያዊያን፣ በህወሓት እጅ ለወደቁ ወገኖቻችን ድጋፍ የሚያሰሙትን ድጋፍ አጠናክረው እንዲቀጥሉ ያሳስባል።
ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ!!!
CategoryEditorial

Thursday, 2 July 2015

Alarm Bells for Ethiopia’s 100% Election Victory – Human Rights Watch


June 24, 2015
(By Felix Horne )

A woman casts her vote at a polling station, as Ethiopia’s national election kicks off in capital Addis Ababa, May 24, 2015.
Elections where a ruling party wins 100 percent of the seats in parliament should always ring alarm bells. Results in Ethiopia from the May 24 general election, released yesterday, are no exception. According to Ethiopia’s National Electoral Board, the ruling Ethiopian People’s Revolutionary Democratic Front (EPRDF) coalition won 546 parliamentary seats (with the 547th seat still to be announced).
The results shouldn’t be seen as a stamp of approval for Prime Minister Hailemariam Desalegn’s government – rather they are the inevitable outcome of a political system in which opposition parties face extraordinary challenges and nearly all avenues for citizens to engage in political debate are closed.
The seeds for this situation were sown years ago. Since the last election in 2010, in which the EPRDF won a mere 99.6 percent of parliamentary seats, political space has been further restricted: the independent media has been decimated, civil society groups virtually eliminated, and peaceful public demonstrations quelled, sometimes by force.
The crackdown on opposition parties and their supporters was the final piece of the puzzle. In the lead-up to the elections, the authorities arrested leading members of the opposition and put them on trial on trumped-up terrorism charges. Political parties reported difficulties in registering candidates and acquiring funds to which they are legally entitled. Security force personnel arrested and harassed people organizing rallies, confiscating their equipment and unfairly denying them permits. Over the last two weeks, several opposition members and candidates have been beaten to death in suspicious circumstances.
International observers were largely absent, choosing not to monitor a vote that provided little opportunity to be independent and effective observers. The African Union was the exception, concluding that the elections were “calm, peaceful, and credible” – a standard very different from being free and fair.
The European Union and the United States, two of Ethiopia’s key allies, were largely silent on the political crackdown. Instead, they congratulated Ethiopia for a “peaceful” election, more concerned with the increasing potential for violence than with a fair electoral landscape. This is short-sighted and dangerous. Authoritarian control rarely provides long-term stability and nearly always compounds significant human rights violations.
For many Ethiopians, the elections confirmed what they already knew: the ruling coalition completely controls all aspects of their daily life and permits no alternative political views. The question is, when will Ethiopia’s allies open their eyes?

Monday, 29 June 2015

The assassination of Samuel Aweke and Tadesse Abraha shall invigorate the struggle for freedom and justice



June 21, 2015
def-thumb“I clearly understand that I may be imprisoned, but my conscience will still be free. I also know that they may kill me, but this is a price that must be paid for freedom. I am passing the torch and I appeal to people of my generation to carry the torch to the gates of freedom”
These were the words of Samuel Aweke, the latest victim of the ever brutal regime in Ethiopia.
Patriotic Ginbot 7, Movement for Unity and Democracy is deeply saddened by yet another brutal assassination of Samuel Aweke and Tadesse Abraha by the TPLF regime. The 29 years old lawyer, Samuel Aweke was a Blue Party member who ran in the May 24 election in his home town of Debre Markos. His political carrier started at the tender age of 19 when he joined Coalition for Unity and Democracy (CUD) in 2005. Samuel Aweke, a young man revered and loved by many, was a proven leader who had endless love for freedom and justice.
Samuel was a community organizer and a columnist for one of the local online newspapers who was in the radar of the TPLF regime for a long time. Days before the May 2015 election, Samuels was brutally beaten by the ruling party cadres in an attempt to deter his candidacy representing the Blue party. During the Beating, the brute cadres repeatedly told Samuel that he can no more practice law in Ethiopia and he may also lose his life if he does not refrain himself from any kind of opposition activities. The courageous Samuel clearly knew that his days on earth were numbered, but he never gave up his struggle for justice and democracy.
Mr. Abraha was a member of the Arena- Medrek party who like Mr. Aweke repeatedly received warnings and death threats from the ruling party cadres. Mr. Abraha, who was choked to death by three plain closed security officers was a true ambassador of freedom and justice. We strongly believe that, it is the love and trust these two heroes earned from millions of Ethiopians and the passion they have for freedom and justice that eventually brought their young and unfulfilled life to a shockingly sad and sudden end.
With a continuously growing financial aid and diplomatic cover by the US, UK and EU, the TPLF regime has been arresting, torturing, and killing innocent Ethiopians for almost a quarter of a century. The Ethiopian people have patiently waited for 24 years hoping that the regime will come to its senses and improve political conditions, but five elections latter, the brutal TPLF regime has 100% control of the parliament and the political space has been totally closed for opposition politics. In the meantime, the arrest, the torture and the killing has continued unabated.
Patriotic Ginbot 7 condemn the brutal killing of these two political activists in its strongest term and to bring such politically motivated killings to an end, we call upon all Ethiopians to rise united against tyranny. Patriotic Ginbot7 believes that the Ethiopian people have the inalienable right to defend themselves from tyranny. This right is enshrined in the Universal Declaration of Human Rights and the constitution of many democratic countries. The Ethiopian people are patient, but it should be understood that patience is not to endlessly wait for something to happen. Patience is how we behave and what alternatives we look while we’re waiting. Patriotic Ginbot 7 strongly believes now the wait is over and the time has come to exercise our inalienable right to rebel against tyranny and oppression. We also believe that the international community will stand with us in our struggle for freedom, justice and democracy.
We shall prevail !
CategoryEnglishPress Release